- Sputnik አፍሪካ, 1920
The Rising South
የዓለም አቀፍ የኃይል ሚዛን እየተቀየረ ባለበት በዚህ ወቅት - ኢትዮጵያን፣ አፍሪካን እና ሌሎችን የሚቀርጹ የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚ እና የማህበራዊ ሃይሎች ወደምንመለከትበት ወደ “ራይዚንግ ሳዉዝ” እንኳን በደህና መጡ፡፡ ደቡባዊ አመለካከቶችን ወደ ዓለም አቀፋዊ ውይይት መድረክ ስናቀርብ የአሰላሳዮችን ፣ የመሪዎችን እና የለዉጥ ፈጣሪዎችን ሃሳብ ያድምጡ።

ቢትኮይን ፣ ባህል እና ደቡባዊው ዓለም፦ የኢትዮጵያ ዲጂታል እድገትና የባህል አንድነት

ቢትኮይን ፣ ባህል እና ደቡባዊው ዓለም፦ የኢትዮጵያ ዲጂታል እድገትና የባህል አንድነት
ሰብስክራይብ
በዚህ የራይዚንግ ሳዉዝ፣ ሁለት ጉልበታም የሆኑና ቀጣናውን የሚቀርጹ ጉዳዮች ላይ ትኩረት እናደርጋለን፤ ቢትኮይን ማልማት እና የባህል ማንሰራራት፡፡
በክፍል አንድ፡ የቢትኮይን ባለሙያው ቃል ካሳ የኢትዮጵያ እያደገ የመጣዉ የኤሌክትሪክ ኃይል የክሪፕቶ ኢንደስትሪውን እንዴት እየመገበው እንደሆነይናገራል፤ በያዝነው ዓመት ብቻ ዘርፉ ከ200 ሚሊየን ዶላር በላይ ገቢ አስገብቷል፡፡
ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ ዛሬ ለም/ቤት አባላትበሰጡት ማብራሪያ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ በቀጣዩ ዓመት ይመረቃል ብለዋል። ይህም ኢትዮጵያ ለምታደርገው የኤሌክትሪክ ኃይል ሉዓላዊነት ወሳኝ እርምጃ ይሆናል። በአፍሪካ ለሚኖራት የዲጂታል ኢኮኖሚ ሚናም ተጨማሪ አቅምን ይሰጣታል፤ እያደገ የመጣውን የቢትኮይን ማልማት ዘርፍም ይጭምራል፡፡
"ኢትዮጵያ ትርፍ ወይም የተረፈ [የኤሌክትሪክ] ሃይል አላት ይባላል […] ስለዚህ የቢትኮይን ማዕድን አልሚዎች ይህን ትርፍ ሃይል መግዛት ይችላሉ። በግምት 3.2 ሳንቲም/ኪሎዋት በሰዓት እየከፈሉ ነው — ከግብር በኋላ እስከ 3.8ሳንቲም ይሆናል።” ሲል ቃል ካሳ ሃሳቡን ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግሯል፡፡
🎨 በክፍል ሁለት፡ ራይዚንግ ሳዉዝ የደቡባ ትብብር ካውንስል ፌስቲቫልን መነሻ አድርጎ፣ የባህል ነጻነትን ስለመቀዳጀት የተለያዩ ሀሳቦችን ራይዚንግ ሳዉዝ በሰፊው ዳስሷል፡፡
የደቡባዊ ትብብር ድርጅት (ኦኤስሲ) ዋና ጸሐፊ ማንሱር ቢን ሙሳላም ስለዚሁ ጉዳይ ሲያነሱ፦
“ድምፃችንን መመለስ አለብን [...] አሳዛኙ ነገር በህዝቦቻችን፣ በአርቲስቶቻችን እና በባህላዊ ተዋንያኖቻችን መካከል እንዴት ድልድይ መገንባት እንዳለብን አለማወቃችን ነው።” ብለዋል፡፡
የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ዴኤታ ረዳት ፕሮፌሰር ነብዩ ባዬ በበኩላቸው፦
አርቲስቶች "በሰሜናዊው ዓለም አስተሳሰቦች የሚመራውን የወጣቶቻችንን ምናብ ለማቅናት መትጋት አለባቸው፡፡” በማለት አሳስበዋል፡፡
ስለ ቢትኮይን 'ማይኒንግ'ም ሆነ ስለ ባህል ሉዓላዊነት በጥልቀት ለመረዳት ይህን በእንግሊዝኛ ቋንቋ የቀረበዉን የራይዚንግ ሳውዝ ፕሮግራም ይከታተሉ!
ፖድካስታችንን በሌሎች አማራጮች ያድምጡ AfripodsDeezerPocket CastsPodcast AddictSpotify
አዳዲስ ዜናዎች
0