ትራምፕ የዩክሬን ጦርነት በፍጥነት የሚቆምበትን ጉዳይ በተመለከተ ለፑቲን እንዳነሱ ረዳታቸው ገለፁ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱትራምፕ የዩክሬን ጦርነት በፍጥነት የሚቆምበትን ጉዳይ በተመለከተ ለፑቲን እንዳነሱ ረዳታቸው ገለፁ
ትራምፕ የዩክሬን ጦርነት በፍጥነት የሚቆምበትን ጉዳይ በተመለከተ ለፑቲን እንዳነሱ ረዳታቸው ገለፁ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 03.07.2025
ሰብስክራይብ

ትራምፕ የዩክሬን ጦርነት በፍጥነት የሚቆምበትን ጉዳይ በተመለከተ ለፑቲን እንዳነሱ ረዳታቸው ገለፁ

ዩሪ ኡሻኮቭ በሁለቱ መሪዎች ንግግር ዙሪያ የሰጧቸው ቁልፍ መግለጫዎች፦

🟠 ፑቲን ሩሲያ የዩክሬን ግጭት በድርድር እንዲፈታ በያዘችው አቋም እንደፀናች ለትራምፕ ገልፀዋል።

🟠 የሩሲያ መሪው ሞስኮ የግጭቱን መንስኤዎች ሁሉ መፍታት አለባቸው የሚለውን አቋም እንደማትተው ለትራምፕ አስታውቀዋል።

🟠 ፑቲን እና ትራምፕ በኢራን እና በመካከለኛው ምስራቅ አጠቃላይ ሁኔታ በዝርዝር ተወያይተዋል።

🟠 ሁለቱ መሪዎች በሶሪያ ያለውን ወቅታዊ ሁኔታ በውይይታቸው አንስተዋል፤ ሞስኮ እና ዋሽንግተን በሶሪያ ዙሪያ ውይይታቸውን ይቀጥላሉ።

🟠 በኃይል እና በህዋ ጥናት ተስፋ ሰጭ በሆኑ የጋራ ኢኮኖሚያዊ ፕሮጀክቶች ላይ ተወያይተዋል።

🟠 ፑቲን እና ትራምፕ በአካል ስለመገናኘት አልተወያዩም።

🟠 መሪዎቹ ግንኙነታቸውን ለመቀጠልና መነጋገር ቢፈልጉ በማንኛውም ጊዜ ስልክ ማንሳት እንደሚችሉ መግባባት ላይ ደርሰዋል።

🟠 ትራምፕ በአሜሪካ ሴኔት የታክስ እና የኢሚግሬሽን ማሻሻያ ረቂቅ ሕግ በተሳካ ሁኔታ ስለመጽደቁ ለፑቲን አንስተዋል።

🟠 የሩሲያው መሪ ለመጪው የአሜሪካ የነፃነት ቀን ለትራምፕ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።

🟠 ፑቲን ሩሲያ በአሜሪካ የመንግሥት ምሥረታ ትልቅ ሚና መጫወቷን አውስተዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0