የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከቢትኮይን ማይኒንግ ከ200 ሚሊየን ዶላር በላይ መሰብሰቡን ገለፀ
20:56 02.07.2025 (የተሻሻለ: 21:04 02.07.2025)
© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱየኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከቢትኮይን ማይኒንግ ከ200 ሚሊየን ዶላር በላይ መሰብሰቡን ገለፀ

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከቢትኮይን ማይኒንግ ከ200 ሚሊየን ዶላር በላይ መሰብሰቡን ገለፀ
ገቢው የተገኘው በማስተላለፊያ መሠረተ ልማቶች እጥረት ምክንያት ይባክን የነበረውን የኤሌክትሪክ ኃይል ለቢትኮይን ማይኒንግ በማዛወር ነው።
‘‘በተያዘው ዓመት በወር ዝቀተኛው ገቢ 25 ሚሊየን ዶላር፤ ከፍተኛው ደግሞ 28 ሚሊየን ዶላር ነው" ሲሉ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኮሚኒኬሽን ዳይሬክተር ሞገስ መኮንን ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል፡፡
ቢትኮይን ማይኒንግ ውስብስብ ስሌቶችን በመጠቀም የክሪፕቶ ግብይቶች የሚረጋገጡበት መንገድ ነው።
ለዚህም ቀንና ሌሊት የሚሠሩ አዳዲስ ዘመናዊ ኮምፒውተሮችን የያዙ መጋዘኖች የሚጠይቅ እንደሆነና ብዙ የኤሌክትሪክ ኃይል እንደሚፈልግ ይነገራል።
በሰው ሰራሽ አስተውህሎት የበለፀገ ምሥል
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X