ኢትዮጵያ ዓለም ዓቀፍ የፋይናንስ ተቋማት ማሻሻያ እንደሚያሻቸው አሳሰበች

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱኢትዮጵያ ዓለም ዓቀፍ የፋይናንስ ተቋማት ማሻሻያ እንደሚያሻቸው አሳሰበች
ኢትዮጵያ ዓለም ዓቀፍ የፋይናንስ ተቋማት ማሻሻያ እንደሚያሻቸው አሳሰበች - Sputnik አፍሪካ, 1920, 02.07.2025
ሰብስክራይብ

ኢትዮጵያ ዓለም ዓቀፍ የፋይናንስ ተቋማት ማሻሻያ እንደሚያሻቸው አሳሰበች

በተመድ የኢትዮጵያ ምክትል ቋሚ መልዕክተኛ አምባሳደር ሳሙኤል ኢሳ የሪፎርም ጥያቄዎቹ የዘላቂ ልማት ተግዳሮቶችን ለመፍታት ቁልፍ እንደሆኑ ተናግረዋል።

በሲቪያ፣ ስፔን እየተካሄደ በሚገኘው አራተኛው ዓለም ዓቀፍ የልማት ፋይናንስ ኮንፍረንስ ጎን ለጎን በተካሄደ ልዩ ስብሰባ የልማት እንቅፋቶች ያሏቸውን ጉዳዮች ዘርዝረዋል፦

🟠የእዳ ጫና፣

🟠የአየር ንብረት ለውጥ ቀውስ እና

🟠በዓለም ላይ እየሰፋ የመጣው የሀገራት የእድገት ልዩነት።

አምባሳደር ሳሙኤል የ "ሲቪያን ስምምነት" ን መተግበር አማራጭ የሌለው ጉዳይ መሆኑንም ገልጸዋል።

ስምምነቱ በዘላቂ ልማት ትግበራ ዙሪያ ያለውን የ4 ትሪሊየን ዶላር ዓመታዊ የፋይናንስ ክፍተት በ10 ዓመት ውስጥ ለማጥበብ ያለመ ሰነድ ነው።

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0