- Sputnik አፍሪካ, 1920
Sovereignty Sources
ዓለም በሉላዊነት ምክንያት ስትተሳሰር ፤ ፕሮግራሙም አፍሪካ ባላት እምቅ የተፈጥሮ ኃብት፣ በማደግ ላይ ባለው የሕዝብ ቁጥሯ ፣ በወጣት ኃይሏ እና በአህጉሪቱ ባሉ አዳዲስ ግኝቶችና የመፍትሄ ሃሳቦች ያላትን የመወዳደር አቅምና ጥቅም በሰፊው ይዳስሳል፡፡ እንኳን ወደ 'ሶቨርኒቲ ሶርስ' ፕሮግራም በደህና መጡ፣

ኒውክለር ኢነርጂ ለሰላማዊ ትሩፋት፡  በኢትዮ-ሩሲያ የትብብር ዓውድ ሲቃኝ – ለጋራ ዕድገት የሚደረግ አጋርነት

ኒውክለር ኢነርጂ ለሰላማዊ ትሩፋት፡  በኢትዮ-ሩሲያ የትብብር ዓውድ ሲቃኝ – ለጋራ ዕድገት የሚደረግ አጋርነት
ሰብስክራይብ
ከዕውቀት ሽግግር እስከ ኢነርጂ ሉዋዓላዊነት፣ ብሎም እስከ ጤናው ዘርፍ - አዲስ ምዕራፍ ተጀምሯል።
የኒውክለር ሳይንስን ለሰላማዊ ጉዳይ የማዋል ቁርጠኝነት በጤናው ዘርፍ አንድ ብሏል።
የሶቨርኒቲ ሶርስስ ፕሮግራም በዛሬው መርሃ ግብሩ ስለኒውክለር ኢነርጂ በኢትዮጵያ እንዲሁም በዘርፉ ከሩሲያ ጋር ስላለ ትብብርና አጋርነት በጥልቀት ለመወያየት ዶ/ር እምሻው ዳምጠው፣ በኢትዮጵያ የኒውክለር ኢነርጂ ሶሳይቲ ዳይሬክተር እንዲሁም ዶ/ር ጥላሁን ተስፋዬ፣ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የፊዚክስ ትምህርት ክፍልየኒውክለር ፊዚክስ ስትሪም ተባባሪ ፕሮፈሰርን ጋብዟቸዋል።
የኒውክለር ኃይል ሰላማዊ ጥቅሞቹ ላይ ለመስራት የሚንቀሳቀሰው የኒዪክሌር ኢነርጂ ሶሳይቲ ሲመሠረት ሩሲያ ስለነበራት ቁልፍ ሚና ዶ/ር እምሻው ሲያስረዱ፦
“በሀገሪቱ የኒውክላር ኢነርጂ ሶሳይቲን መሥርተናል። በወቅቱ ሩሲያ በተለይም በሮሳተም በኩል እውቀት ተኮር ገለፃዎችን በመሥጠት ጭምር ብዙ ረድታናለች። በመሥረታው ጊዜ ብቻ ሳይሆን በምረቃ ሥነ ሥርዓቱም ላይ እንደዛው፣ እናም ከዚያ ጊዜ ጀምሮ ትብብሩ እንደቀጠለ ነው'' ሲሉ ተናግረዋል።
ዶ/ር ጥላሁን በበኩላቸው በዘርፉ ስላሉ መጠነ ሰፊ ድጋፎች ሲያብራሩ፦
“የትምህርት፣ ስልጠና፣ መሠረተ ልማት ማስፋፋት እንዲሁም የቴክኖሎጂ ሽግግር ድጋፎችን ያደርጉልናል። ይህ ሁሉ ከሩሲያኖች የሚመጡ የተቀናጁ ማዕቀፎች ናቸው። የዓለም አቀፍ የኒውክለር ትብብራቸው ዘላቂ አጋርነት ነው'' ብለዋል።
በሀገራቱ መካከል የተፈጠረው አጋርነት ኢትዮጵያ በዘርፉ የቴክኖሎጂ መሠረተ ልማቶችን እንድታጎለብት ያስችላታል።
የበለጠ ለመረዳት ይፈልጋሉ? በዚሁ የሶቨርኒቲ ሶርስስ ፕሮግራም የተዳሰሱ የኒውክለር ኢነርጂ ልማት በኢትዮጵያ እንዲሁም የኢነርጂ ሶሳይቲ አጠቃላይ ሁኔታና እንቅስቃሴ ሃሳቦችን ይከታተሉ!
አዳዲስ ዜናዎች
0