ኢትዮጵያ ጎረቤቶቿን በኤሌክትሪክ ኃይል በማስተሳሰር ለነጠላ የኢነርጂ ገበያ ትግበራ መሠረት ሆናለች ሲል የአፍሪካ ኅብረት አስታወቀ
15:14 01.07.2025 (የተሻሻለ: 15:34 01.07.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
ኢትዮጵያ ጎረቤቶቿን በኤሌክትሪክ ኃይል በማስተሳሰር ለነጠላ የኢነርጂ ገበያ ትግበራ መሠረት ሆናለች ሲል የአፍሪካ ኅብረት አስታወቀ
የድርጅቱ የመሠረተ ልማትና ኢነርጂ ዳይሬክተር ካሙጊሻ ካዛውራ ኢትዮጵያ ከሱዳን፣ ጁቡቲ፣ ኬኒያ እና ከቀሪ ጎረቤቶቿ ጋር የኃይል ትስስር እየፈጠረች እንደሆነ እውቅና ሰጥተዋል፡፡
ይህም ለአፍሪካ ኅብረት የነጠላ ኢነርጂ ገበያ ትግበራ አቅም እየሆነች መምጣቷን የሚያሳይ ነው ማለታቸውን የሀገር ውስጥ ሚዲያ ዘግቧል፡፡
ድርጅቱ ለሁለት ቀናት የሚቆይ የአፍሪካ ነጠላ የኤሌክትሪክ ገበያ አጀንዳ ከፍተኛ የቴክኒክ ግምገማ አካሂዷል።
የዘንድሮው መድረክ የአፍሪካ ኅብረት አጀንዳ 2063 የነጠላ ኢነርጂ ገበያ የዕቅድ የአፈፃጸም ትግበራ ሂደት የታየበት ነው።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X