የክሮከስ ኮንሰርት አዳራሽ ጥቃት በዩክሬን እንደተቀነባበረ ፈፀሚዎቹ አመኑ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱየክሮከስ ኮንሰርት አዳራሽ ጥቃት በዩክሬን እንደተቀነባበረ ፈፀሚዎቹ አመኑ
የክሮከስ ኮንሰርት አዳራሽ ጥቃት በዩክሬን እንደተቀነባበረ ፈፀሚዎቹ አመኑ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 29.06.2025
ሰብስክራይብ

የክሮከስ ኮንሰርት አዳራሽ ጥቃት በዩክሬን እንደተቀነባበረ ፈፀሚዎቹ አመኑ

ሞስኮ አቅራቢያ በሚገኘው የክሮከስ አዳራሽ ለ147 ሰዎች ሞት ምክንያት የሆነውን ጥቃት የፈፀሙቱ፤ ከጥቃቱ ጀርባ ዩክሬን እንዳለችበት በእምነት ቃላቸው እንደገለፁ ስፑትኒክ ያገኘው ማስረጃ አሳይቷል።

ከጥቃቱ በኋላ ታጣቂዎቹ ወደ ኪዬቭ ለመሸሽ አቅደው እንደነበርና እያንዳንዳቸው አንድ ሚሊየን ሩብል (12 ሺህ 743 የአሜሪካ ዶላር) ቃል እንደተገባላቸው ተናግረዋል። ጥቃት ፈጻሚዎቹ በዩክሬናውያን አማካኝነት የጦር መሳሪያ እንደቀረበላቸውም ገልፀዋል።

መጋቢት 13፣ 2016 ዓ.ም ታጣቂዎች ወደ ሙዚቃ አዳራሹ ገብተው በታዳሚዎች ላይ ተኩስ በመክፈት እና ቲያትር ቤቱን በእሳት በማቀጣጠል 147 ሰዎች ሲገደሉ ወደ 500 የሚጠጉ ቆስለዋል። ሦስት ተጠርጣሪዎች እስካሁን አልተገኙም።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0