ሩሲያ ሰላም ወዳድ ሕዝቦች በኢስታንቡል የሚካሄደውን ድርድር ይደግፋሉ ብላ እንደምትጠብቅ ዲፕሎማቱ ተናገሩ
13:43 29.06.2025 (የተሻሻለ: 14:04 29.06.2025)
© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱሩሲያ ሰላም ወዳድ ሕዝቦች በኢስታንቡል የሚካሄደውን ድርድር ይደግፋሉ ብላ እንደምትጠብቅ ዲፕሎማቱ ተናገሩ

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ሩሲያ ሰላም ወዳድ ሕዝቦች በኢስታንቡል የሚካሄደውን ድርድር ይደግፋሉ ብላ እንደምትጠብቅ ዲፕሎማቱ ተናገሩ
በቪየና የጦር መሳሪያ ቁጥጥር ድርድር የሩሲያ ልዑክ መሪ ዩሊያ ዝዳኖቫ "በአሜሪካ፣ በሳዑዲ አረቢያ እና በቱርክ ድጋፍ ቀጥተኛ የሩሲያ-ዩክሬን ንግግሮች እንዲቀጥሉ ሁኔታዎች ተመቻችተዋል" ሲሉ ለስፑትኒክ ተናግረዋል።
"ግን ይሄ ጅማሬ ነው። አንዳንድ ኃይሎች ግማሽ እርምጃዎችን በመውሰድ ወይም ሂደት ሙሉ በሙሉ የማደናቀፍ ከፍተኛ ፍላጎት እንዳላቸው እናያለን” ብለዋል።
በድርድሩ መጨረሻ ሞስኮ እና ኪዬቭ ሁሉን አቀፍ ስምምነት መፈረም እንዳለባቸው ዲፕሎማቷ አፅዕኖት ሰጥተዋል።
ከሶስት ዓመት በኋላ ሩሲያ እና ዩክሬን ግንቦት 8 ለመጀመሪያ ጊዜ ድርድር ያደረጉ ሲሆን ሁለተኛ ዙር ድርድራቸውን ግንቦት 25 በቱርክ አካሂደዋል። የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የቀጣዩ ዙር የድርድር ቀን በቅርቡ እንደሚወሰን ባለፈው ሳምንት አስታውቋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X