ኢትዮጵያ ወሳኝ የሕክምና አቅርቦቶችን ለማድረስ ድሮኖችን መጠቀም ልትጀምር ነው
18:13 28.06.2025 (የተሻሻለ: 18:34 28.06.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ኢትዮጵያ ወሳኝ የሕክምና አቅርቦቶችን ለማድረስ ድሮኖችን መጠቀም ልትጀምር ነው
የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር የሚመራው ፕሮጀክት ወሳኝ የሕክምና አቅርቦቶችን በፍጥነት በማድረስ የጤና ቀውሶችን ለመከላከል ያለመ ነው።
🟠የሕክምና ማጓጓዣ ድሮኖቹ በ30 ደቂቃ 100 ኪሎሜትር መብረር ይችላሉ፣
🟠30 ኪሎግራም ጭነት የመሸከም አቅም አላቸው፣
🟠በአንዳንድ ክልሎች በተካሄደ ሙከራ ውጤታማ ሆነዋል።
በተጨማሪም በወባ መራቢያ አካባቢዎች ኬሚካል የሚረጩ ድሮኖችን ለመጠቀም ታቅዷል።
ድሮኖቹ በቅርቡ በዓለም ጤና ድርጅት ትብብር በጤና ጥበቃ ሚኒስቴር በተዘጋጀው ዓለም አቀፍ የጤና ፈጠራና ጥራት ጉባኤ ላይ መቅረባቸውን የሀገር ውስጥ ሚዲያ ዘግቧል።
በሰው ሰራሽ አስተውህሎት የበለፀገ ምሥል
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X