ትራምፕ ለኢራን መንፈሳዊ መሪ ክብር እንዲሰጡ አባስ አራግቺ ጠየቁ
13:28 28.06.2025 (የተሻሻለ: 13:34 28.06.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ትራምፕ ለኢራን መንፈሳዊ መሪ ክብር እንዲሰጡ አባስ አራግቺ ጠየቁ
ትራምፕ ከቴህራን ጋር የኒውክሌር ስምምነት ለመድረስ የሚሹ ከሆነ በሚሊየን የሚቆጠሩ የአያቶላህ አሊ ካሜኔይ ታማኝ ደጋፊዎችን የሚያስከፋ ቃል መጠቀማቸውን ማቆም አለባቸው ሲሉ የኢራኑ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ተናግረዋል።
በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የኢራን ተወካይ አሚር ሰኢድ ኢራቫኒም እስራኤል እና ዩናይትድ ስቴትስ በቅርቡ ካሜኔይ ላይ የሰነዘሩትን ዛቻ ድርጅቱ እንዲያወግዝ ጠይቀዋል።
"ከፍተኛ ባለሥልጣናት በግድ የለሽነትና ሆን ብለው የሰነዘሩት ማስፈራሪያ የአንድ ሀገር ፖለቲካዊ ነፃነት ወይም የግዛት አንድነት ላይ ስጋት መፍጠር ወይም ኃይል መጠቀም የሚከለክለውን የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ቻርተር በግልፅ የሚጥስ ነው" ሲሉ ተወካዩ በድብዳቤያቸው ላይ አስፍረዋል።
ትራምፕ ካሜኔይ የት እንዳሉ "በትክክል ያውቁ እንደነበር፤ ነገር ግን ለአሜሪካ እና እስራኤል ጦር እንዳይገደሉ ትዕዛዝ በመስጠታቸው አያቶላውን "ከአሰቃቂ ሞት" እንደታደጉ ተናግረዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X