ፑቲን ሩሲያ ከዩክሬን ጋር ሶስተኛ ዙር ድርድር ለማድረግ ዝግጁ ነች አሉ
18:01 27.06.2025 (የተሻሻለ: 18:24 27.06.2025)
© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
ፑቲን ሩሲያ ከዩክሬን ጋር ሶስተኛ ዙር ድርድር ለማድረግ ዝግጁ ነች አሉ
የሩሲያ እና የዩክሬን ተደራዳሪዎች በጉዳይ ዙሪያ እየተገናኙ እንደሆነ ፕሬዝዳንቱ ተናግረዋል።
አክለውም የልዑካን ቡድኑ መሪዎች ቀጣዩ ድርድር የሚደረግበትን ቀን ለመወሰን በውይይት ላይ ናቸው ብለዋል።
ፕሬዝዳንቱ የሰጧቸው ሌሎች መግለጫዎች፦
🟠 የዩክሬን እና ሩሲያ ረቂቅ ሰነዶች ፍፁም ተቃራኒ ናቸው፡፡
🟠 ሩሲያ እና ዩክሬን ለሰላም ስምምነቱ ያዘጋጇቸው የመግባቢያ ሰነድ ረቂቆች በሶስተኛው ድርድር ዙር የውይይት ትኩረት መሆን አለባቸው፡፡
🟠 ሩሲያ ተጨማሪ 3 ሺህ የዩክሬን ወታደሮችን አስክሬን ለመመለስ ዝግጁ ናት፡፡
🟠 ፑቲን ኔቶ ወደ ምሥራቅ "አንድ ኢንች እንኳን "እንደማይስፋፋ ቢናገረም በተከታታይ ዙር በመስፋፋቱ ሩሲያ "ተታልላለች" ሲሉ ተናግረዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X