በትግራይ የሚገኘው ታሪካዊው የአል-ነጃሺ መስጂድ የእድሳት ሥራው መጠናቀቁ ተገለፀ
14:23 26.06.2025 (የተሻሻለ: 14:34 26.06.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
በትግራይ የሚገኘው ታሪካዊው የአል-ነጃሺ መስጂድ የእድሳት ሥራው መጠናቀቁ ተገለፀ
በሰሜኑ ጦርነት ወቅት ከፍተኛ ጉዳት የደረሰበት ከውቅሮ ከተማ ወጣ ብሎ የሚገኘው ጥንታዊው የኢትዮጵያ ቅርስ፤ ባለፉት 9 ወራት እድሳት ሲደረግለት እንደነበረ የክልሉ ባሕልና ቱሪዝም ቢሮ አስታውቋል።
የቢሮው ምክትል ኃላፊ ኃይላይ በየነ የመስጂዱ የእድሳት ሥራ ከቱርክ ልማት ኤጀንሲ በተገኘ ድጋፍ መከናወኑን ለአሐዱ ራዲዮ ተናግረዋል፡፡
አክለውም "በአሁኑ ጊዜ ከመስጂዱ የተዘረፉ ቅርሶችን ቁጥር የማጣራት ሥራ እየተሠራ ነው" ብለዋል።
እድሳቱ የትግራይን የቱሪዝም ዘርፍ በማነቃቃት ረገድ ጉልህ ሚና እንደሚጫወትም ነው የተነገረው።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

© telegram sputnik_ethiopia
/