በኢራን-እስራኤል ግጭት ዙሪያ የዛሬ ረፋድ መረጃዎች

በኢራን-እስራኤል ግጭት ዙሪያ የዛሬ ረፋድ መረጃዎች
🟠 በኢራን እና በእስራኤል መካከል የተደረሰው የተኩስ አቁም ስምምነት ይፋ ከተደረገ በኋላ ሁለቱም ወገኖች ስምምነቱን በመጣስ ቢወነጃጀሉም ተግባራዊነቱ እንደቀጠለ ነው።
🟠 የኢራን ባለሥልጣናት የብሔራዊ ደህንነትን የሚጎዳ ነው ተብሎ በሚታሰብ በማንኛውም ድርጊት ላይ እርምጃ ለማጠናከር እየተንቀሳቀሱ ነው።
🟠 የአካባቢው መገናኛ ብዙኃን እንደዘገቡት ጦርነቱ በጀመረ በ12 ቀናት ውስጥ በመላው ኢራን ውስጥ ቢያንስ 700 የስለላ ወንጀል ተጠርጣሪዎች ተይዘዋል።
🟠 የተባበሩት መንግሥታት የኒውክሌር ተቆጣጣሪ ኤጀንሲ ኃላፊ ራፋኤል ግሮሲ እንደተናገሩት አብዛኛው የኢራን የበለፀገ ዩራኒየም ቀደም ብሎ በመዘዋወሩ በአሜሪካ-እስራኤል ጥቃቶች ሳይጎዳ ሳይቀር ቀርቷል። ፍተሻዎች በመታገዳቸው ኤጀንሲው ይህንን ማረጋገጥ የሚችልበት መንገድ የለውም ብለዋል።
🟠 የአሜሪካ ጥቃቶች በኢራን ላይ ውጤት እንዳላመጡ የሚያመለክት የስለላ ሪፖርት መውጣቱን ተከትሎ የሲአይኤ ኃላፊ ጆን ራትክሊፍ በሰጡት ምላሽ ያለምንም ማስረጃ የኢራን የኒውክሌር መርሃ ግብር ለዓመታት ወደኋላ እንደተመለሰ ተናግረዋል።
🟠 የወጣው የመከላከያ ኢንተለጀንስ ኤጀንስ ሪፖርት ሚስጥራዊ መረጃዎችን ለኮንግረስ ማጋራት በሚያስችለው ካፕኔት ሲስተም ላይ እንደተለቀቀ አንድ ከፍተኛ ባለሥልጣን ለሲኤንኤን ተናግረዋል። ኋይት ሀውስም መረጃ ማጋራቱን ለመቀነስ እንዳሰበ ተዘግቧል።
🟠 የአሜሪካ ሴኔት በኢራን ዙሪያ የሚቀርብለት የስለላ ግኝቶች ማብራሪያ ሃሙስ ከሰዓት ይካሄዳል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X