በኢራን-እስራኤል ግጭት ዙሪያ የዛሬ ረፋድ መረጃዎች

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱበኢራን-እስራኤል ግጭት ዙሪያ የዛሬ ረፋድ መረጃዎች
በኢራን-እስራኤል ግጭት ዙሪያ የዛሬ ረፋድ መረጃዎች - Sputnik አፍሪካ, 1920, 26.06.2025
ሰብስክራይብ

በኢራን-እስራኤል ግጭት ዙሪያ የዛሬ ረፋድ መረጃዎች

🟠 በኢራን እና በእስራኤል መካከል የተደረሰው የተኩስ አቁም ስምምነት ይፋ ከተደረገ በኋላ ሁለቱም ወገኖች ስምምነቱን በመጣስ ቢወነጃጀሉም ተግባራዊነቱ እንደቀጠለ ነው።

🟠 የኢራን ባለሥልጣናት የብሔራዊ ደህንነትን የሚጎዳ ነው ተብሎ በሚታሰብ በማንኛውም ድርጊት ላይ እርምጃ ለማጠናከር እየተንቀሳቀሱ ነው።

🟠 የአካባቢው መገናኛ ብዙኃን እንደዘገቡት ጦርነቱ በጀመረ በ12 ቀናት ውስጥ በመላው ኢራን ውስጥ ቢያንስ 700 የስለላ ወንጀል ተጠርጣሪዎች ተይዘዋል።

🟠 የተባበሩት መንግሥታት የኒውክሌር ተቆጣጣሪ ኤጀንሲ ኃላፊ ራፋኤል ግሮሲ እንደተናገሩት አብዛኛው የኢራን የበለፀገ ዩራኒየም ቀደም ብሎ በመዘዋወሩ በአሜሪካ-እስራኤል ጥቃቶች ሳይጎዳ ሳይቀር ቀርቷል። ፍተሻዎች በመታገዳቸው ኤጀንሲው ይህንን ማረጋገጥ የሚችልበት መንገድ የለውም ብለዋል።

🟠 የአሜሪካ ጥቃቶች በኢራን ላይ ውጤት እንዳላመጡ የሚያመለክት የስለላ ሪፖርት መውጣቱን ተከትሎ የሲአይኤ ኃላፊ ጆን ራትክሊፍ በሰጡት ምላሽ ያለምንም ማስረጃ የኢራን የኒውክሌር መርሃ ግብር ለዓመታት ወደኋላ እንደተመለሰ ተናግረዋል።

🟠 የወጣው የመከላከያ ኢንተለጀንስ ኤጀንስ ሪፖርት ሚስጥራዊ መረጃዎችን ለኮንግረስ ማጋራት በሚያስችለው ካፕኔት  ሲስተም ላይ እንደተለቀቀ አንድ ከፍተኛ ባለሥልጣን ለሲኤንኤን ተናግረዋል። ኋይት ሀውስም መረጃ ማጋራቱን ለመቀነስ እንዳሰበ ተዘግቧል።

🟠 የአሜሪካ ሴኔት በኢራን ዙሪያ የሚቀርብለት የስለላ ግኝቶች ማብራሪያ ሃሙስ ከሰዓት ይካሄዳል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0