የኢራን-እስራኤል ፍጥጫ፦ የሰኔ 18 ጠዋት ወቅታዊ ዜናዎች

የኢራን-እስራኤል ፍጥጫ፦ የሰኔ 18 ጠዋት ወቅታዊ ዜናዎች
🟠 የኢራን ፓርላማ ሀገሪቷ ከዓለም አቀፉ የኒውክሌር ተቆጣጣሪ ኤጄንሲ ጋር የነበረውን ትብብር የሚያቋርጥ ረቂቅ ሕግ ያፀደቀ ሲሆን በዚህም የኤጀንሲው ሠራተኞች የኒውክሌር ተቋማትን ለመፈተሽ ሀገሪቱን መጎብኘት አይችሉም፡፡
🟠 ከሰኔ 6 ጀምሮ ኢራን ውስጥ 700 ሰዎች ለእስራኤል በመሰለል ተጠርጥረው ታስረዋል ሲል የሀገር ውስጥ መገናኛ ብዙኃን ዘግበዋል።
🟠 የኢራን ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አባስ አራግቺ ሰኞ ዕለት ከሩሲያ ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ጋር ያደረጉት ውይይት ጥሩ እንደነበር ገልፀው ሞስኮ የአሜሪካ እና የእስራኤል ጥቃትን በተመለከተ ጥብቅ አቋም መያዟን አስታውቀዋል።
🟠 የአሜሪካ ጥቃት የኢራንን የኒውክሌር መርሃ ግብር ዋና ዋና ክፍሎች አላጠፋም፤ ነገር ግን እድገቱን ለወራት "ወደ ኋላ እንደጎተተው" አንዳንድ የአሜሪካ ሚዲያዎች የደህንነት መረጃዎችን ጠቅሰው ዘግበዋል።
🟠 በምላሹ የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ አሜሪካ በኢራን ላይ የወሰደችውን ጥቃት ለማጣጣል ሞክረዋል ሲሉ ሚዲያዎቹን ከሰዋቸዋል፡፡
🟠 የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ልዩ መልዕክተኛ ስቲቭ ዊትኮፍ ዋሽንግተን ከኢራን ጋር ሁሉን አቀፍ የሰላም ስምምነት ላይ መድረስ እንደምትችል እምነታቸውን ገልጸዋል።
🟠 የምዕራባውያን መገናኛ ብዙኃን በኢራን ሰላማዊ የኒውክሌር ተቋማት ላይ የሚደረጉ ጥቃቶች በታሪክ የመጀመሪያው እንደሆኑ ባለመዘገባቸው ሙያዊ ወንጀል ሠርተዋል ሲሉ የሩሲያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ማሪያ ዛካሮቫ ተናግረዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X