ኢትዮጵያ እና አንጎላ በተመድ የፀጥታው ምክር ቤት ማሻሻያዎች ዙሪያ ተወያዩ
11:59 24.06.2025 (የተሻሻለ: 12:04 24.06.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ኢትዮጵያ እና አንጎላ በተመድ የፀጥታው ምክር ቤት ማሻሻያዎች ዙሪያ ተወያዩ
ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ ከወቅቱ የአፍሪካ ኅብረት ሊቀመንበር እና የአንጎላ መሪ ጃዎ ሎሬንሶ ጋር በሁለቱ ሀገራት የሁለትዮሽ ግኑኝነት እና አፍሪካ በዓለም መድረክ ያላትን ሚና ማጎልበት ላይ ያተኮረ ምክክር አድርገዋል።
በአንጎላ ርዕሰ መዲና ሉዋንዳ ከተካሄደው የአፍሪካ-አሜሪካ የቢዝነስ ፎረም ጎን ለጎን ተገናኝተው ባካሄዱት ውይይት፤ አሁን ዓለም ላይ ለሚታዩ ችግሮች መፍትሄ በማፈላለግ አፍሪካ ግንባር ቀደም ሚና መጫወት በምትችልበት መንገድ ዙሪያ አስተያየት ተለዋውጠዋል።
በሁለቱ ሀገራት መካከል የተቋቋመው የሚኒስትሮች የጋራ ኮሚቴ በፍጥነት ወደ ሥራ እንዲገባ መግባባት ላይ እንደደረሱም የሀገር ውስጥ ሚዲያ ዘግቧል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X