ኬንያ ከፖለቲካ ጦማሪ ሞት ጋር በተያያዘ የፖሊስ አባላትን ጨምሮ ስድስት ሰዎች ላይ ክስ መሠረተች
11:33 24.06.2025 (የተሻሻለ: 11:54 24.06.2025)
© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱኬንያ ከፖለቲካ ጦማሪ ሞት ጋር በተያያዘ የፖሊስ አባላትን ጨምሮ ስድስት ሰዎች ላይ ክስ መሠረተች

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ኬንያ ከፖለቲካ ጦማሪ ሞት ጋር በተያያዘ የፖሊስ አባላትን ጨምሮ ስድስት ሰዎች ላይ ክስ መሠረተች
በ31 ዓመቱ መምህርና ጦማሪ አልበርት ኦጅዋንግ ሞት የተጠረጠሩት ተከሳሾች በዛሬው ዕለት ፍርድ ቤት እንደሚቀርቡ የኬንያ የዐቃቤ ሕግ ዳይሬክተር ፅሕፈት ቤት አስታውቋል።
በፖሊስ ቁጥጥር ሥር እያለ መሞቱን ተከትሎ በናይሮቢ ማዕከላዊ የንግድ አካባቢዎች ከፍተኛ ተቃውሞ መቀስቀሱ ይታወሳል። ተቃዋሚዎች የምክትል ኢንስፔክተር ጄኔራል ኤሊዩድ ላጋት ተግባር ለኦጅዋንግ ሞት ምክንያት ነው በማለት እንዲታሰሩ ጠይቀዋል። ላጋት ከኃላፊነታቸው ቢነሱም ብዙዎች ይህ በቂ አይደለም እያሉ ነው።
ፖሊስ ያቀረባቸው የቅደመ አስከሬን ምርመራ ውጤቶች ኦጅዋንግ "ወድቆ እንደሞተ" ቢገልጹም፤ የመንግሥት የአስከሬን ምርመራ ግን ጥቃት እና አካላዊ ጉዳት መኖሩን አሳይቷል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X