- Sputnik አፍሪካ, 1920
The Rising South
የዓለም አቀፍ የኃይል ሚዛን እየተቀየረ ባለበት በዚህ ወቅት - ኢትዮጵያን፣ አፍሪካን እና ሌሎችን የሚቀርጹ የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚ እና የማህበራዊ ሃይሎች ወደምንመለከትበት ወደ “ራይዚንግ ሳዉዝ” እንኳን በደህና መጡ፡፡ ደቡባዊ አመለካከቶችን ወደ ዓለም አቀፋዊ ውይይት መድረክ ስናቀርብ የአሰላሳዮችን ፣ የመሪዎችን እና የለዉጥ ፈጣሪዎችን ሃሳብ ያድምጡ።

ከተረጅነት ወደ አጋርነት፦ የምዕራባውያን ዕርዳታ መቀነስ እና ብሪክስ ይዞት የመጣው ዕድል በኢትዮጵያ

ከተረጅነት ወደ አጋርነት፦ የምዕራባውያን ዕርዳታ መቀነስ እና ብሪክስ ይዞት የመጣው ዕድል በኢትዮጵያ
ሰብስክራይብ
የዓለም የምግብ ፕሮግራም የኢትዮጵያ ዳይሬክተር የሆኑት ዝላታን ሚሊሲች አሜሪካ እና ሌሎች ምዕራባዊያን ሀገራት ለዓለም የምግብ ፕሮግራም የሚያደርጉትን ዕርዳታ በመቀነሳቸው ምክንያት በኢትዮጵያ ውስጥ ሊደረግ ከታሰበው ዕርዳታ በግማሽ ያህል እንደሚያንስ ተናግረዋል። የሚቀነሰው የዕርዳታ መጠን በአሀዝ ሲገለጽ 222 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር ወይም 28 ቢሊየን ብር ገደማ እንደሚሆን ጠቁመዋል።
በዚህኛው የራይዚንግ ሳውዝ ዝግጅታችን በኢትዮጵያ የኢኮኖሚክስ ማህበር ውስጥ ከፍተኛ ተመራማሪ እንዲሁም የፖርትነርሺፕ እና ኮሚኒኬሽን ዳይሬክተር ዶ/ር አቡሌ መሀሪ ጋር በጉዳዩ ዙሪያ ቆይታ አድርገናል፡፡
በዘላቂነት ራስን በምግብ ስለመቻል፣ ዶ/ር አቡሌ
“በኢትዮጵያ የ222 ሚሊዮን ዶላር የምግብ እርዳታ እጥረት የውጭ ድጋፍ ላይ ከመጠን በላይ መደገፍ ዘላቂነት እንደሌለው የሚያሳይ አስከፊ እውነታ ጎልቶ ያሳያል። ዓለም አቀፍ እርዳታ በአስቸኳይ ጊዜያት ወሳኝ ሚና ቢጫወትም የአንድ አገር የምግብ ሥርዓት መሠረት መሆን የለበትም” ሲሉ አስረድተዋል።
ኢትዮጵያ የብሪክስ አባል በመሆኗ ልታገኝ ስለምትችላቸው ጥቅሞችም ሲያስረዱ ዶ/ር አቡሌ
“በዚህ ጉዞ የብሪክስ ትብብር ለውጥ ያመጣል። ብዙውን ጊዜ በአጭር ጊዜ እፎይታ ላይ ከሚያተኩሩ ባህላዊ ለጋሾች በተለየ የብሪክስ አገሮች በረጅም ጊዜ አቅም ላይ ኢንቨስት ያደርጋሉ። በራሳችን እንድንቆም የሚያስችሉንን የቴክኖሎጂ ሽግግር፣ ሥልጠና እና መሠረተ ልማቶችን ይሰጣሉ” ብለዋል።
ስለ ምግብ ሉዓላዊነት እና ኢትዮጵያ በብሪክስ አባልነት ልታገኝ ስለምትችላቸው ድጋፎች የበለጠ ለማወቅ ይህንን የራይዚንግ ሳውዝ ዝግጅት ይከታተሉ።
አዳዲስ ዜናዎች
0