“ኔታንያሁ አሜሪካን የሚያስከፍል ጦርነት ውስጥ ከተዋታል” በተመድ የኢራን ቋሚ መልዕክተኛ
10:59 23.06.2025 (የተሻሻለ: 11:04 23.06.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
“ኔታንያሁ አሜሪካን የሚያስከፍል ጦርነት ውስጥ ከተዋታል” በተመድ የኢራን ቋሚ መልዕክተኛ
ልዑኩ አሚር ሰይድ ኢራቫኒ በተመድ የፀጥታው ምክር ቤት አስቸኳይ ስብሰባ ላይ ንግግር አድርገዋል።
የንግግራቸው ዋና ዋና ነጥቦች የሚከተሉት ናቸው፦
የተከሰተው ጉዳይ በተባበሩት መንግሥታት ታሪክ ላይ ጠባሳ የጣለ ነው።
እስራኤል እና አሜሪካ በኢራን ላይ የሚፈፅሟቸው ጥቃቶች አረመኔያዊ ናቸው።
በጠላታችን አሜሪካ እና በወኪሏ እስራኤል ላይ ራሳችንን የመከላከል መብታችንን እናስጠብቃለን።
ኢራን ሰላም ወዳድ እና የኒውክሌር ጦር መሳሪያ ባይኖራትም፤ በሁለት የኒውክሌር ጦር መሳሪያ በታጠቁ ሀገራት ተጠቅታለች።
አሜሪካ በኢራን ላይ ያቀረበቻቸው ክሶች ፖለቲካዊ እና መሠረተ ቢስ ናቸው።
በትክክለኛው የታሪክ ጎን ለመቆም የመረጡትን እና የአሜሪካን ጥቃት ያወገዙ አባላትን እናደንቃለን።
እስራኤል የምዕራባውያንን ክፉ ሥራ መፈፀም ሲሳናት፤ ትራምፕ አስጸያፊውን አጀንዳ በራሳቸው እንዲተገብሩ ተገደዋል።
አሜሪካ ኔታንያሁንን ለመጠበቅ የራሷን ደህንነት በግዴለሽነት ለመሰዋት ደግማ ወስናለች።
የጦር ሠራዊታችን ተገቢውን ምላሽ የሚሰጥበትን ጊዜ፣ መንገድ እና መጠን ይወስናል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X