“የተባበሩት መንግሥታት እኛ እንደምንፈልገው ዲሞክራሲያዊ እና ወካይ አይደለም” ሲሉ የደቡብ አፍሪካ ባለሥልጣን ተናገሩ

ሰብስክራይብ

“የተባበሩት መንግሥታት እኛ እንደምንፈልገው ዲሞክራሲያዊ እና ወካይ አይደለም” ሲሉ የደቡብ አፍሪካ ባለሥልጣን ተናገሩ

“ተመድ ለዓለም ሰላም ለማምጣት ማዕከላዊ ሚና ነበረው፤ ነገር ግን የራሱ ውስንነቶች አሉበት” ሲሉ የደቡብ አፍሪካ ምክትል ፕሬዝዳንት ተጠባባቂ ቃል አቀባይ ኪዝ ኮዛ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል።

እንደ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት፣ ዓለም አቀፉ የወንጀለኛ ፍርድ ቤት (አይሲሲ) ወይም ዓለም አቀፉ የፍትህ ፍርድ ቤት (አይሲጄ) ያሉ ዓለም አቀፍ ተቋማትን የማሻሻል ፍላጎት እየጨመረ መምጣቱን እንዲሁም አንዳንድ ሀገራት ፈራሚ እንኳን አለመሆናቸውን ከ #SPIEF2025 ፎረም ጎን ለጎን ጠቁመዋል።

“እያደጉ ያሉ ሀገራት በሰሜን እና በደቡብ እንዲሁም ባደጉ እና ባላደጉ ሀገራት መካከል ፍትሐዊ ውክልና እንዲኖር የተባበሩት መንግሥታት ድርጅትን ጨምሮ ሁሉም ዓለም አቀፋዊ ተቋማት መሻሻል አለባቸው በማለት ሲናገሩ ቆይተዋል” ሲሉ ኮዛ አክለው ገልፀዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0