የኢራን አብዮታዊ ዘብ አሜሪካ ለፈፀመችው ጥቃት እንድትጸጸት እናደርጋለን በማለት ዛተ

ሰብስክራይብ

የኢራን አብዮታዊ ዘብ አሜሪካ ለፈፀመችው ጥቃት እንድትጸጸት እናደርጋለን በማለት ዛተ

የዩናይትድ ስቴትስ ጥቃት ኢራን ራሷን የመከላከል ሕጋዊ መብቷን እንድትጠቀም እና ምላሽ እንድትሰጥ እንዲሁም አሜሪካ በድርጊቷ እንድትጸጸት ለማድረግ ሁሉንም አማራጮች እንድትጠቀም ያስችላታል ሲል የኢራን ብሄራዊ ማሰራጫ የአብዮታዊ ዘቡን መግለጫ  ጠቅሶ ዘግቧል።

በመካከለኛው ምስራቅ የሚገኙ የአሜሪካ የጦር ሰፈሮች ቁጥር፣ ቦታ እና ስፋት የአሜሪካን ጥንካሬ ብቻ ሳይሆን ተጋላጭነቷን የሚጨምሩ ደካማ ጎኖቿ ናቸው ሲል መግለጫው አክሏል።

የኢራን አብዮታዊ ዘብ የእስራኤልን መሠረተ ልማቶች እና ስትራቴጂካዊ ጠቀሜታ ያላቸውን ተቋማት ማጥቃቱን እንደሚቀጥል ገልጿል።

በማህበራዊ የትስስር ገፆች የሚዘዋወሩ ምስሎች  በቴል አቪቭ አካባቢ የኢራን ጥቃቶች ያስከተሉትን ጉዳቶች ያሳያሉ

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0