አሜሪካ የኢራንን የኒውክሌር ተቋማት ትናንት ምሽት አጥቅታለች። እስከ ዛሬ ጠዋት የተሠሙ ቁልፍ ክስተቶች፦

አሜሪካ የኢራንን የኒውክሌር ተቋማት ትናንት ምሽት አጥቅታለች። እስከ ዛሬ ጠዋት የተሠሙ ቁልፍ ክስተቶች፦
የአሜሪካ ወታደራዊ እርምጃ፦
▪የአሜሪካ ቦምብ ጣይ ጄቶች ቅዳሜ ከምሽቱ 5:00 ገደማ በኢራን የፎርዶውና ናታንዝ የኒውክሌር ተቋማት ላይ ጥቃት አድርሰዋል።
▪አሜሪካ ጥቃቶቹ መንግሥት ለመገልበጥ ያለሙ እንዳልሆኑ በቀጥታ ለኢራን ገልጻለች።
▪ትራምፕ ኢራን የሰላም ጥሪውን ካልተቀበለች በድጋሚ ጥቃት ለመፈፀም ዝግጁ ነን ብለዋል።
የኢራን ምላሽ፦
▪ቴህራን በፎርዶው ጥቃት እንደሚሰነዘር በመጠበቅ ቁሳቁሶችን እንዳወጣችና ሊቀለበስ የማይችል ጉዳት እንዳልደረሰ ገልጻለች።
▪አሜሪካ ኢራን ላይ ጦርነት ከፍታለች ሲል የሀገሪቱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል።
▪ጥቃቱ እስራኤል ኢራን ላይ የፈፀመችውን ጥቃት በማቀድ አሜሪካ ተሳታፊ እንደነበረች ያሳያል ብሏል።
▪የአሜሪካ ጥቃት መጠነ ሰፊ መዘዞች እንደሚያስከትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ገልጸዋል።
▪ኢራን አስቸኳይ የጸጥታው ምክር ቤት ስብሰባ ጠርታለች።
የጨረር ፍሰት፦ የኢራን አቶሚክ ኢነርጂ ድርጅት ምንም ዓይነት የጨረር ፍሰት እንዳልተከሰተ ያወጣውን መግለጫ ዓለም አቀፉ የአቶሚክ ኤጀንሲ አረጋግጧል።
የእስራኤል ምላሽ፦
▪ኔታንያሁ የኢራን ኒውክሌር አቅምን እንደሚያጠፉ የገቡት የቆየ ቃል መፈጸሙን ተናግረዋል።
▪ከአሜሪካ ጥቃት በሗላ እስራኤል የአየር ክልሏን ዘግታለች።
ዓለም አቀፍ ምላሽ፦
▪የተመድ ዋና ጸሃፊ ጥቃቱ የቀጣናውን ሁኔታ በማባባስ ለዓለም ሰላም ስጋት ሆኗል ሲሉ አውግዘዋል።
▪ሁቲዎች በቀይ ባሕር በአሜሪካ መርከቦች ላይ የበቀል ጥቃት ዛቻ አሰምተዋል።
▪ኢራቅና ሳዑዲ አረቢያ የአሜሪካን ጥቃት አውግዘዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X