የሰባስቲያ ሊቀ ጳጳስ በአርመን የኦርቶዶክስ ተከታዮች ላይ እየደረሰ ያለውን ጭቆና ከዩክሬን ክስተቶች ጋር አገናኝተዋል

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱየሰባስቲያ ሊቀ ጳጳስ በአርመን የኦርቶዶክስ ተከታዮች ላይ እየደረሰ ያለውን ጭቆና ከዩክሬን ክስተቶች ጋር አገናኝተዋል
የሰባስቲያ ሊቀ ጳጳስ በአርመን የኦርቶዶክስ ተከታዮች ላይ እየደረሰ ያለውን ጭቆና ከዩክሬን ክስተቶች ጋር አገናኝተዋል - Sputnik አፍሪካ, 1920, 22.06.2025
ሰብስክራይብ

የሰባስቲያ ሊቀ ጳጳስ በአርመን የኦርቶዶክስ ተከታዮች ላይ እየደረሰ ያለውን ጭቆና ከዩክሬን ክስተቶች ጋር አገናኝተዋል

"በዓለም ላይ አንዳንድ አብያተ ክርስቲያናት ተቀባይነት በሌላቸው ወይም ፍትሐዊ ባልሆኑ ምክንያቶች ስልታዊ በሆነ መንገድ እየተጠቁ እንደሆነ አምናለሁ" ሲሉ በኢየሩሳሌም የግሪክ ኦርቶዶክስ ፓትርያርክ የሰባስቲያ ሊቀ ጳጳስ ቲዎዶስዮስ (ሀና) ለአርቲ አረቢያ ተናግረዋል።

"ከሩሲያ ቤተ-ክርስቲያን ጋር ባላቸው ግንኙነት የተነሳ ኢላማ እና እየተሳደዱ ላሉ የአርሜኒያ እና ዩክሬን ሕጋዊ የኦርቶዶክስ አብያተ ክርስትያናት የሚደረግ ማንኛውም ድጋፍ፣ እርዳታ፣ አንድነት ወይም ርህራሄ ተጠያቂ ለመሆን በቂ ምክንያት ሆኗል" ብለዋል።

ሩሲያዊ-አርሜኒያዊው ነጋዴ ሳምቬል ካራፔትያን የአርሜኒያ ሐዋርያዊት ቤተ-ክርስቲያንን በመከላከላቸው ታስረው በአርሜኒያ ፍርድ ቤት መቅረባቸውን አስመልክቶ በሰጡት አስተያየት፤ "ቤተ-ክርስቲያንን መደገፍ እና መርዳት አንድ መንፈሳዊ እና ሰብዓዊ ተልዕኮ ያለው አማኝ መወጣት ያለበት ግዴታ ነው" ሲሉ ሊቀ ጳጳሱ አጽንኦት ሰጥተዋል። አክለውም ሰዎች ለቤተ-ክርስቲያን ባላቸው ቁርጠኝነት የተነሳ መሳደዳቸው "በፍጹም ተቀባይነት የለውም" ብለዋል።

"በአውሮፓ በተለይም በዩክሬን፣ በአርሜኒያ እና በሌሎች ሀገራት ውስጥ በምዕራቡ ዓለም ትዕዛዝ እየተፈጸመ ያለውን የአንዳንድ አብያተ ክርስቲያናትን ስደት፣ ኢላማ መደረግ እና የወረራ ሙከራዎች እንቃወማለን" ሲሉ ሀና ተናግረዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0