በኢትዮጵያ ከአምስት ዓመት በኋላ ሁሉም የመንግሥት ተቋማት አግልሎታቸውን በበይነ መረብ አማካኝነት እንደሚሰጡ ተነገረ
20:25 20.06.2025 (የተሻሻለ: 20:34 20.06.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
በኢትዮጵያ ከአምስት ዓመት በኋላ ሁሉም የመንግሥት ተቋማት አግልሎታቸውን በበይነ መረብ አማካኝነት እንደሚሰጡ ተነገረ
እቅዱ የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ አካል እንደሆነ የኢኖቬሽን ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡
ውጥኑ የቢሮክራሲ እና የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ይፈታሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ ተገልጿል፡፡ የኢትዮጵያ ብሔራዊ መታወቂያ (ፋይዳ) ለእቅዱ ምቹ ሁኔታን ይፈጥራል መባሉን ጠቅሶ የሀገር ውስጥ ጋዜጣ ዘግቧል፡፡
ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ የመንግሥት ተቋማትን ብቻ ሳይሆን የግሉን ዘርፍም እንደሚያካትት ተጠቁሟል፡፡
በሰው ሰራሽ አስተውህሎት የበለፀገ ምሥል
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X