ፑቲን ሩሲያ የዩክሬን ሱሚ ከተማን የመቆጣጠር ግብ የላትም ነገር ግን ጉዳዩ ከጨዋታ ወጪ አይደለም ብለዋል
19:08 20.06.2025 (የተሻሻለ: 19:24 20.06.2025)
© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱፑቲን ሩሲያ የዩክሬን ሱሚ ከተማን የመቆጣጠር ግብ የላትም ነገር ግን ጉዳዩ ከጨዋታ ወጪ አይደለም ብለዋል

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ፑቲን ሩሲያ የዩክሬን ሱሚ ከተማን የመቆጣጠር ግብ የላትም ነገር ግን ጉዳዩ ከጨዋታ ወጪ አይደለም ብለዋል
የሩሲያ መሪ በዩክሬን ዙሪያ የሰጡት መግለጫ ክፍል ሁለት፡-
▪ በሱሚ ክልል ውስጥ ያለው የሩሲያ በፈር ዞን ከ8-12 ኪሎ ሜትር ይደርሳል።
▪የሩሲያ ጦር በሱሚ ክልል የሚወስደው እርምጃ ግጭቱ በሚቀጥልበት ሁኔታ ላይ ይመሠረታል።
▪ ሩሲያ ከዩክሬን ጋር በሚያዋስናት ድንበር ላይ የፀጥታ ቀጣና እንድትፈጥር ተገድዳለች፤ ይህም ቀድሞውንም በቂ ያልሆነውን የዩክሬን ኃይል ትኩረት ከፋፍሏል።
▪ ዩክሬን የውጊያ ዝግጁነቷን አጥታለች፤ የሠራዊቱ የሰው ኃይል 47 በመቶው ብቻ ነው።
▪ ኪዬቭ የኩርስክ ክልልን በማጥቃት በራሷ ላይ ችግር ፈጥራለች።
▪ የዩክሬን ታጣቂ ኃይሎች በሩሲያ ኩርስክ ግዛት በሰላማዊ ሰዎች ላይ ጭምር ብዙ ወንጀሎችን ፈጽመዋል።
▪ዩክሬናውያን ከውጭ ስፖንሰሮቻቸው ተጨማሪ ገንዘብ ይፈልጋሉ፤ ግማሹን ይሰርቃሉ።
▪ ኪዬቭ በኩርስክ ክልል ላይ ያደረሰችው ጥቃት ከምዕራባውያን ስፖንሰሮች እርዳታ የማግኘት ፖለቲካዊ ዓላማ ነበረው።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X