- Sputnik አፍሪካ, 1920
The Rising South
የዓለም አቀፍ የኃይል ሚዛን እየተቀየረ ባለበት በዚህ ወቅት - ኢትዮጵያን፣ አፍሪካን እና ሌሎችን የሚቀርጹ የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚ እና የማህበራዊ ሃይሎች ወደምንመለከትበት ወደ “ራይዚንግ ሳዉዝ” እንኳን በደህና መጡ፡፡ ደቡባዊ አመለካከቶችን ወደ ዓለም አቀፋዊ ውይይት መድረክ ስናቀርብ የአሰላሳዮችን ፣ የመሪዎችን እና የለዉጥ ፈጣሪዎችን ሃሳብ ያድምጡ።

የወደፊቱ የዲጂታል ዓለም ፦ አፍሪካ በቴክኖሎጂ ዘመን ያላት ድምፅ

የወደፊቱ የዲጂታል ዓለም ፦ አፍሪካ በቴክኖሎጂ ዘመን ያላት ድምፅ
ሰብስክራይብ
🌍 አፍሪካ በዲጂታሉ ዓለም መስቀለኛ መንገድ ላይ ቆማለች። የምዕራባውያን ቴክኖሎጂ እና የሰው ሰራሽ አስተውሎት የበላይነት በያዙበት በዚህ ወቅት ጥያቄው ግልጽ ነው፡- አፍሪካ ማንነቷን ጠብቃ ዲጂታል ዓለሙን በመምራት ቀዳሚ መሆን ትችላለችን ?
በዚህ የራይዚንግ ሳውዝ ክፍል፣ ዶ/ር ብርሃኑ እሸቴ፣ በሚቺጋን ዩኒቨርሲቲ፣ ዩ.ኤስ.ኤ ረዳት ፕሮፌሰር ፣ ዶ/ር ዮአኪም ጂ. ፐርሶን፣ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የስነ ጥበብ እና ዲዛይን ትምህርት ቤት ረዳት ፕሮፌሰር እና ዶ/ር ዝናወርቅ አሰፋ፣ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የኢትዮጵያ ቋንቋዎች እና ባህል ማዕከል ኃላፊ በአንገብጋቢዉ ጉዳይ ላይ ሃሳባቸውን አጋርተውናል።
ዶ/ር ዝናወርቅ ፣ “ባህላችንን ለዓለም በተለይም ለ ብሪክስ አባል ሀገራት ለማካፈል ራሳችንን ማዘጋጀት አለብን […] ፕሮጀክቶችን፣ የፕሮፖዛል ሃሳቦችን አዘጋጅተን ለ ብሪክስ ሀገራት ማህበረሰብ ማቅረብ አለብን።” በማለት ተናግረዋል፡፡
ዶ/ር ዮአኪም የአካባቢ ዩኒቨርሲቲዎች ወጣቶችን በምርምር እንዲሳተፉ እና [የአካባቢ] ቁሳቁሶችን በመሰብሰብ ረገድ ትልቅ ሚና መጫወት ይችላሉ ሲሉ መክረዋል።
ዶ/ር ብርሃኑ፣ “አፍሪካውያን ጉዳዩን አጥብቀው መያዝ አለባቸው […] አንድን ቴክኖሎጂ ስትጠቀም ራስህን፣ ቋንቋህን፣ ባህልህን፣ ታሪክህን እና የቃል ወጎችህን ታያለህ?” ሲሉ አፍሪካ ተወዳዳሪ መሆን የምትችለው መሰረቷን ባለመርሳት ጭምር ነው ሲሉ ተናግረዋል።
ሃሳቡን በጥልቀት ለመረዳት ይህን በእንግሊዝኛ ቋንቋ የቀረበዉን የራይዚንግ ሳውዝ ፕሮግራም ይከታተሉ!
ፖድካስታችንን በሌሎች አማራጮች ያድምጡ AfripodsDeezerPocket CastsPodcast AddictSpotify
አዳዲስ ዜናዎች
0