ፑቲን ከቻይና ፕሬዝዳንት ሺ ጂንፒንግ ጋር በስልክ ተነጋገሩ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱፑቲን ከቻይና ፕሬዝዳንት ሺ ጂንፒንግ ጋር በስልክ ተነጋገሩ
ፑቲን ከቻይና ፕሬዝዳንት ሺ ጂንፒንግ ጋር በስልክ ተነጋገሩ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 19.06.2025
ሰብስክራይብ

ፑቲን ከቻይና ፕሬዝዳንት ሺ ጂንፒንግ ጋር በስልክ ተነጋገሩ

በመካከለኛው ምስራቅ ስላለው ሁኔታ መወያታቸውን የሩሲያው ፕሬዝዳንት ረዳት አስታውቀዋል።

በዩሪ ኡሻኮቭ የተሰጡ ሌሎች ቁልፍ መግለጫዎች፦

🟠 ሩሲያ እና ቻይና የተባበሩት መንግሥታት ቻርተርን የሚጥሱ የእስራኤል ድርጊቶችን በፅኑ አውግዘዋል።

🟠 በተጨማሪም ሞስኮ እና ቤጂንግ በመካከለኛው ምስራቅ ያለውን ሁኔታ በኃይል መፍታት እንደማይቻል ያምናሉ።

🟠 ፑቲን አስፈላጊ ከሆነ ሩሲያ የመካከለኛው ምስራቅ ግጭትን ለማሸማገል ዝግጁ መሆኗን አረጋግጠዋል።

🟠 የሩሲያ እና የቻይና መሪዎች በሚቀጥሉት ቀናት ከመካከለኛው ምስራቅ ጋር በተያያዘ ግንኙነቶችን እንዲያደርጉ እና መረጃ እንዲለዋወጡ ለሁለቱ ሀገራት አስተዳደሮች እና አገልግሎቶች ትዕዛዝ ለመስጠት ተስማምተዋል።

🟠 ፑቲን እና ሺ ጂንፒንግ የቡድን 7 የመሪዎች ስብሰባ ውጤቶችን ተወያይተዋል። በስብሰባው ተሳታፊዎች መካከል የነበሩትን አስቸጋሪ ጉዳዮችም ተነስተዋል።

🟠 ለዘለንስኪ የቡድን 7 የመሪዎች ስብሰባ በውጭ ሀገር ካደረጋቸው ጉዞዎች ሁሉ ስኬታማው እንዳልነበር ተነስቷል።

🟠 ፑቲን እና ሺ ጂንፒንግ ነሐሴ 27 በቻይና ተገናኝው ይወያያሉ።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0