ኢትዮጵያ 10 ቢሊየን ዶላር ይፈጃል የተባለ ፈጣን መንገድ ለመገንባት እቅድ እንዳላት ተገለፀ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱኢትዮጵያ 10 ቢሊየን ዶላር ይፈጃል የተባለ ፈጣን መንገድ ለመገንባት እቅድ እንዳላት ተገለፀ
ኢትዮጵያ 10 ቢሊየን ዶላር ይፈጃል የተባለ ፈጣን መንገድ ለመገንባት እቅድ እንዳላት ተገለፀ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 17.06.2025
ሰብስክራይብ

ኢትዮጵያ 10 ቢሊየን ዶላር ይፈጃል የተባለ ፈጣን መንገድ ለመገንባት እቅድ እንዳላት ተገለፀ

የኢትዮጵያ መንግሥት 2 ሺህ ኪሎ ሜትር የሚያካልል የፈጣን መንገድ መሠረተ ልማት ለመገንባት ማቀዱን ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ከገንዘብ ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ባሳተመው አዲስ የኢንቨስትመንት “ስምምነት መጽሐፍ” ውስጥ ተገልጿል።

በውጥኑ የተካተቱ የመንገድ መስመሮች፦

🟠 አዲስ አበባ–ኮምቦልቻ–ደሴ፦ 352.2 ኪ.ሜ (2.32 ቢሊየን ዶላር)፣

🟠 አዲስ አበባ–ጂማ፦ 345.5 ኪ.ሜ (2.03 ቢሊየን ዶላር)፣

🟠 አዲስ አበባ–ደብረ ማርቆስ፦ 317.6 ኪ.ሜ (1.64 ቢሊየን ዶላር)።

ፕሮጀክቱን በመንግሥትና በግሉ ዘርፍ ትብብር እንዲሁም በዓለም አቀፍ ተጫራቾች ለመተግበር መታቅዱን የሀገር ውስጥ ሚዲያ ዘግቧል፡፡

በሰው ሰራሽ አስተውህሎት የበለፀገ ምሥል

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0