አልጄሪያ በ2026 በዱረም ስንዴ ምርት ራሷን እንደምትችል አስታወቀች

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱአልጄሪያ በ2026 በዱረም ስንዴ ምርት ራሷን እንደምትችል አስታወቀች
አልጄሪያ በ2026 በዱረም ስንዴ ምርት ራሷን እንደምትችል አስታወቀች - Sputnik አፍሪካ, 1920, 16.06.2025
ሰብስክራይብ

አልጄሪያ በ2026 በዱረም ስንዴ ምርት ራሷን እንደምትችል አስታወቀች

የሀገሪቱ የግብርና ሚኒስትር ዩሴፍ ቾርፋ ይህ ክብረ ወሰን የሆነ የምርት እድገት የተመዘገበዉ በተሻሻለ የግብርና ስትራቴጂ ምክንያት መሆኑን ገልፀዋል።

እ.ኤ.አ በ2024/2025 የሚመረተው ሰብል በደቡባዊ ክልሎች በአንድ ሄክታር እስከ 80 ኩንታል የሚደርስ ምርት እንደሚያስገኝና በሰሜናዊ የሀገሪቱ ክፍል ደግሞ ከፍተኛ መሻሻል እንደሚታይ አስታውቀዋል።

ስኬቱን ያመጡ ምክንያቶች፦

🟠የተሻሻለ የመሬት አጠቃቀም እና አርሶ አደሮች ትምህርት፣

🟠ለአካባቢው የአየር ንብረት ተስማሚ የሆኑ የስንዴ ዝርያዎችን በማስተዋወቅ፣

🟠ዘመናዊ የግብርና መሠረተ ልማት።

የሚጠበቁ ውጤቶች፦

🟠በገቢ ምርት ላይ ጥገኝነትን መቀነስ፣

🟠የውጭ ምንዛሪ ክምችትን መጠበቅ፣

🟠የሀገሪቱን የምግብ ሉዓላዊነት ማጠናከር።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0