ዩክሬን እና አውሮፓ ሞስኮ ላይ ውስብስብ እና ደም አፋሳሽ ትንኮሳዎችን ለመፈፀም እየተዘጋጁ መሆናቸውን የሩሲያ የውጭ መረጃ አገልግሎት አስታወቀ
14:59 16.06.2025 (የተሻሻለ: 15:04 16.06.2025)
© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱዩክሬን እና አውሮፓ ሞስኮ ላይ ውስብስብ እና ደም አፋሳሽ ትንኮሳዎችን ለመፈፀም እየተዘጋጁ መሆናቸውን የሩሲያ የውጭ መረጃ አገልግሎት አስታወቀ

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ዩክሬን እና አውሮፓ ሞስኮ ላይ ውስብስብ እና ደም አፋሳሽ ትንኮሳዎችን ለመፈፀም እየተዘጋጁ መሆናቸውን የሩሲያ የውጭ መረጃ አገልግሎት አስታወቀ
ይህ እየሆነ ያለው ዩክሬን በጦር ግንባር ችግሮች እየተባባሱባት እና "የዩክሬን ማሕበረሰብ ከመጋረጃ ጀርባ የሞራል ድካም" በገጠመው ጊዜ ነው ብሏል አገልግሎቱ በመግለጫው።
የስለላ ድርጅቱ በአሁኑ ወቅት ዩክሬናውያን ከብሪታኒያ ጋር በመሆን በባልቲክ ባሕር ላይ ትንኮሳ ለመሠንዘር እየተዘጋጁ ነው ብሏል። ከሁኔታዎች አንዱ በዩናይትድ ስቴትስ የባሕር ኃይል መርከብ ላይ በሩሲያ የሚላከክ የቶርፔዶ ጥቃት መፈጸምን ያካትታል።
የዩክሬን ወገን የሶቪየት-ሩሲያ ቶርፔዶዎችን ለእንግሊዞች አስረክቧል። አንዳንዶቹ ከአሜሪካ መርከብ “በአስተማማኝ ርቀት” እንዲፈነዱ የታቀደ ሲሆን አንደኛው ግን እንደማይፈነዳና ለሩሲያ “የጥፋት ተግባር” ማስረጃ ሆኖ ለሕዝብ እንደሚቀርብ አገልግሎቱ ግልጿል፡፡
የዩክሬን የጸጥታ ኃይሎች እቅዱን ለማስፈጸም መዘጋጀታቸውንም ነው መግለጫው ያመለከተው።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X