ጊኒ ለሕገ-መንግሥታዊ ሕዝበ ውሳኔ በመዘጋጀት ላይ መሆኗን አስታወቀች
14:01 16.06.2025 (የተሻሻለ: 14:24 16.06.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ጊኒ ለሕገ-መንግሥታዊ ሕዝበ ውሳኔ በመዘጋጀት ላይ መሆኗን አስታወቀች
ፕሬዝዳንት ማማዲ ዶምቦያ መጪውን የሕገ-መንግሥት ማሻሻያ ሕዝበ ውሳኔ የሚቆጣጠር "የአጠቃላይ ምርጫዎች ዳይሬክቶሬት" የተሠኘ ልዩ አካል መቋቋሙን አስታውቀዋል።
መስከረም 11 እንዲካሄድ ቀነ ቀጠሮ የተቀመጠለት የሕዝበ ውሳኔ እ.ኤ.አ በ2021 ከተካሄደው መፈንቅለ መንግሥት በኋላ ሀገሪቱ ወደ ሕገ-መንግሥታዊ ሥርዓት ለመመለስ በምታደርገው ጥረት ትልቅ እርምጃ ነው።
የአዲሱ አካል ዋና ዋና ዓላማዎች የሚከተሉትን ያካትታሉ፦
ሕዝበ ውሳኔው ግልጽና ሁሉን አቀፍ መሆኑን ማረጋገጥ።
በብሔራዊ መዝገብ ላይ በመመሥረት የባዮሜትሪክ የምርጫ መዝገብ ማዘጋጀት እና ማሻሻል።
ምርጫውን ለመጠበቅ ልዩ የፀጥታ ኃይል እንዲቋቋም መተባበር።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X