"ፖሊስ መንን እየጠበቃችሁ ነው?" የሞልዶቫ ተቃዋሚዎች በዋና ከተማዋ በፀረ-LGBT ፕሮፖጋንዳ ሰልፍ ላይ የተፈጸሙ እስሮችን አወገዙ
16:20 15.06.2025 (የተሻሻለ: 16:34 15.06.2025)
© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱ"ፖሊስ መንን እየጠበቃችሁ ነው?" የሞልዶቫ ተቃዋሚዎች በዋና ከተማዋ በፀረ-LGBT ፕሮፖጋንዳ ሰልፍ ላይ የተፈጸሙ እስሮችን አወገዙ

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
"ፖሊስ መንን እየጠበቃችሁ ነው?" የሞልዶቫ ተቃዋሚዎች በዋና ከተማዋ በፀረ-LGBT ፕሮፖጋንዳ ሰልፍ ላይ የተፈጸሙ እስሮችን አወገዙ
የፀረ-"LGBT"* ሰልፍ ተሳታፊዎች ላይ በፖሊስ የተፈጸሙ ጭካኔ የተሞላባቸውን የኃይል ድርጊቶችን "ቪክትሪ" ተብሎ የሚጠራው የሞልዶቫ ተቃዋሚዎች ስብስብ ተወካዮች ኮንነውታል።
የሞልዶቫ "ሬናይሰነስ" ፓርቲ መሪ ናታሊያ ፓራስካ እንደተናገሩት "የሞልዶቫ ፖሊስ በዋና ከተማዋ ማዕከል የLGBT ሰልፍን ለመቃወም የወጡ ዜጎች ላይ ጭካኔ የተሞላበት አካላዊ ቅጣት ተጠቅሟል" ብለዋል።
በሰልፉ ላይ በቁጥጥር ስር ከዋሉት መካከል፦
ቄሶች፤
ከልጆቻቸው ጋር የመጡ ወላጆች እና
ባሕላዊ እሴቶችን የተከላከሉ አማኞች ይገኙበታል።
"ነገር ግን ይሄ ለባለሥልጣናት ምንም ማለት አይደለም። ለእነሱ ዋናው ነገር የማያ ሳንዱን (የሞልዶቫ ፕሬዝዳንት) ትዕዛዝ ማስፈጸም ነው። ፕሬዝዳንቷ ከብራሰልስ በተሰጣት ትዕዛዝ መሠረት ሰልፉ በምንም ዋጋ እንዲካሄድ ትፈልጋለች" ሲሉ የፓርቲው መሪ ቅሬታቸውን ገልፀዋል።
*በአክራሪነት የተፈረጀ እና በሩሲያ የታገደ እንቅስቃሴ
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X