ፑቲን እና ትራምፕ ቅዳሜ በስልክ እንደተወያዩ የፕሬዝዳንቱ ረዳት ተናገሩ
20:03 14.06.2025 (የተሻሻለ: 20:24 14.06.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ፑቲን እና ትራምፕ ቅዳሜ በስልክ እንደተወያዩ የፕሬዝዳንቱ ረዳት ተናገሩ
▪ የፑቲን እና ትራምፕ ውይይት ጠቃሚ እንደነበርና መሪዎቹ በመካከለኛው ምስራቅ ስላለው አስከፊ ሁኔታ እንደመከሩ የሩሲያው ፕሬዝዳንት ረዳት ዩሪ ኡሻኮቭ ገልፀዋል።
▪ የሩሲያው መሪ ትናንት ከኢራን ፕሬዝዳንት እና ከእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ጋር ስላደረጉት የስልክ ውይይት ለትራምፕ አጋርተዋል።
▪ ፑቲን ለትራምፕ በኢራን የኒውክሌር ዶሴ ላይ ለሁሉም ተቀባይ የሆኑ ስምምነቶችን ለማግኘት ሩሲያ ያቀረበችውን ሃሳብ አስታውሰዋል።
▪ ትራምፕ በመካከለኛው ምስራቅ ያለውን ሁኔታ በጣም አሳሳቢ ሲሉ ገልፀውታል። ፕሬዝዳንቶቹ በኢራን የኒውክሌር መርሃ ግብር ዙሪያ ወደሚደረገው ድርድር መመለስን ከጨዋታ ውጪ አላደረጉም።
▪ ፑቲን ከዩክሬን ጋር የተደረሠውን የኢስታንቡል ስምምነት ትግበራ በተመለከተ ለአሜሪካው መሪ ገለጻ አድርገዋል።
▪ እንደ ፑቲን ገለጻ ሩሲያ ከዩክሬን ጋር ያላትን ድርድር ለመቀጠል ዝግጁ ነች።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X