የኢራን እና በእስራኤል ግጭት አሁናዊ መረጃዎች፦

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱየኢራን እና በእስራኤል ግጭት አሁናዊ መረጃዎች፦
የኢራን እና በእስራኤል ግጭት አሁናዊ መረጃዎች፦ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 14.06.2025
ሰብስክራይብ

የኢራን እና በእስራኤል ግጭት አሁናዊ መረጃዎች፦

የደረሱ ጉዳቶች፦

ኢራን፡ 78 ሰዎች ሲገደሉ 320 ሰዎች ቆስለዋል።

እስራኤል፡ ቢያንስ 3 ሰዎች ሲሞቱ 91 ሰዎች ቆስለዋል

የኢራን የኒውክሌር ተቋማትና ሠራተኞች፦

▫እስራኤል 9 የኢራን የኒውክሌር ባለሙያዎችን ገድላለች።

▫ጥቃቶቹ በፎርዶውና ኢስፋሃን የኒውክሌር ጣቢያዎች ውስን ጉዳት አድርሰዋል።

የኢራን መልሶ መጥቃት እርምጃዎች፦

▫ኢራን በ4 ዙር ከ200 በላይ ሚሳኤሎችን አስወንጭፋለች።

▫የእስራኤል ጦር ዋና መሥሪያ ቤት ተመቷል።

▫ኢራን የእስራኤል ጦር ዕዝና የኤሌክትሮኒክስ ጦርነት ስርዓቶችን መትታለች።

▫25% የኢራን ሚሳኤሎች የእስራኤል የአየር መቃወሚያን አልፈዋል።

የቀጠሉ የእስራኤል ኦፕሬሽኖች፦

▫ በታብሪዝ የነዳጅ ማጣሪያዎች ፍንዳታዎች ተሠምተዋል።

▫ጥቃቱ በተለያዩ ሥፍራዎች የባላስቲክ ሚሳኤል ማስወንጨፊያዎችን መቷል።

▫አራት የእስራኤል ድሮኖች ኮራማባድ አቅራቢያ ተመትተዋል።

▫በዛንጃን 3 የኢራን አብዮታዊ ዘብ አባላት ተገድለዋል።

▫በምዕራብ ኢራን የማሽነሪ ፋብሪካ ተመቷል።

▫የኢራን አየር ክልል እሁድ ድረስ ተዘግቶ ይቆያል።

ይፋዊ መግለጫዎች እና ማስፈራሪያዎች፦

▫በተመድ የኢራን ልዑክ የእስራኤልን ድርጊት “መንግሥታዊ ሽብርተኝነት” ብለውታል።

▫ቴህራን አሜሪካ፣ ፈረንሳይና እንግሊዝ ለእስራኤል ድጋፍ ከሠጡ ቀጣናዊ ንብረቶቻቸው ኢላማ እንደሚሆኑ አስጠንቅቃለች።

▫የእስራኤል ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጥቃቶች “ለቀናት ወይም ለሳምንታት” ሊቆዩ እንደሚችሉ ተናግረዋል።

▫የመከላከያ ሚኒስትር ኢራን ጥቃቶቿን ከቀጠለች እስራኤል “ቴህራንን እንደምታቃጥል” አስጠንቅቀዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0