በኢትዮጵያ ባለፉት 10 ወራት 110 የገጠር ቀበሌዎች የኤሌክትሪክ አገልግሎት ተጠቃሚ ሆኑ
18:13 13.06.2025 (የተሻሻለ: 18:34 13.06.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
በኢትዮጵያ ባለፉት 10 ወራት 110 የገጠር ቀበሌዎች የኤሌክትሪክ አገልግሎት ተጠቃሚ ሆኑ
በቀጣይ ሁለት ወራት ወስጥ ተጨማሪ 30 የገጠር ቀበሌዎች መብራት ያገኛሉ ሲሉ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት አስታውቋል።
በበጀት ዓመቱ በሁለት ቢሊየን ብር ወጪ ከዋናው ቋት ውጪ ያሉ 140 የገጠር ቀበሌዎች የኤሌክትሪክ አገልግሎት እንዲያገኙ ለማድረግ እቅድ ተይዟል።
ከኤሌክትሪክ ማሰራጫ ርቀው የሚገኙ አካባቢዎችን በሶላር የኃይል አማራጭ የኤሌክትሪክ አገልግሎት ተጠቃሚ የማድረግ ሥራዎች እየተከናወኑ እንደሆነ የተቋሙን ኃላፊ ጠቅሶ የሀገር ውስጥ ጋዜጣ ዘግቧል።
በሰው ሰራሽ አስተውህሎት የበለፀገ ምሥል
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X