ኢትዮጵያ የአኩሪ አተር ተረፈ ምርት ወደ ቻይና መላክ ልትጀምር ነው
16:09 13.06.2025 (የተሻሻለ: 16:24 13.06.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ኢትዮጵያ የአኩሪ አተር ተረፈ ምርት ወደ ቻይና መላክ ልትጀምር ነው
በቻይና የኢትዮጵያ አምባሳደር ተፈራ ደርበውና የቻይና የጉምሩክ አጠቃላይ አስተዳደር ምክትል ሚኒስትር ዋንግ ልንግጁን በቻይና ቻንግሻ ከተማ በተካሄደው በአራተኛው የቻይና-አፍሪካ የኢኮኖሚና ንግድ ኤክስፖ የጎንዮሽ ስብሰባ ላይ ስምምነቱን ፈርመዋል።
በቻይና የኢትዮጵያ አምባሳደር ተፈራ ደርበው ስምምነቱ ለኢትዮጵያ አዲስ የገበያ እድል እንደሚያሰፋ እና ወደ ቻይና የሚላኩ ምርቶችን ከፍ እንደሚያደርግ ገልጸዋል።
በተመሳሳይ የኢትዮጵያ ቡናን እሴት ጨምሮ ለቻይና ገበያ ለማቅረብ የሚያስችል የመግባቢያ ስምምነት ቻንግሻ ሳተርንበርድ ኮፊ ከተባለ ኩባንያ ጋር ተፈርሟል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱ
