ቻይና 321 ሺህ ዶዝ የኮሌራ መከላከያ ክትባት ለኢትዮጵያ ለገሰች
16:40 11.06.2025 (የተሻሻለ: 17:04 11.06.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ቻይና 321 ሺህ ዶዝ የኮሌራ መከላከያ ክትባት ለኢትዮጵያ ለገሰች
የጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ የቻይና ድጋፍ ተላላፊ እና መከላከል የሚቻሉ በሽታዎችን በመዋጋት ረገድ ዓለም አቀፍ ትብብር ያለውን ጠቀሜታ ያሳያል ሲሉ በርክክቡ ወቅት ተናግረዋል፡፡
የኮሌራ ወረርሽኝ በተለይም መፈናቀልና ድርቅ በደረሰባቸው እንዲሁም መሠረተ ልማት በተጓደለባቸው አካባቢዎች አሁንም ስጋት እንደሆነ መናገራቸውን ጠቅሶ የሀገር ውስጥ ሚዲያ ዘግቧል፡፡
የቻይና አምባሳደር ቼን ሃይ በበኩላቸው ቻይና እና ኢትዮጵያ በጤና አጠባበቅ ዙሪያ የረጅም ጊዜ ትብብር እንዳላቸው ገልጸው፤ ቤጂንግ ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የህክምና ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል ገልጸዋል፡፡
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱ
