የኢትዮጵያ መንግሥት ለ2018 ዓ.ም 1.93 ትሪሊየን ብር ረቂቅ በጀት አቀረበ
16:45 10.06.2025 (የተሻሻለ: 17:04 10.06.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የኢትዮጵያ መንግሥት ለ2018 ዓ.ም 1.93 ትሪሊየን ብር ረቂቅ በጀት አቀረበ
የገንዘብ ሚኒስትር አሕመድ ሺዴ ወጪው የ10 ዓመቱን መሪ የልማት እቅድ ታሳቢ ባደረገ መልኩ እንደተዘጋጀ ተናግረዋል።
ረቂቅ በጀቱ 1.2 ትሪሊየን ብር ለመደበኛ ወጪ፣ 415 ቢሊየን ብር ለካፒታል ወጪ፣ 315 ቢሊየን ብር ለክልል መንግሥታት ድጋፍ እንዲሁም 14 ቢሊየን ብር ለክልሎች የዘላቂ ልማት ግቦች ማስፈፀሚያ ድጋፍ እንደሚውል ገልጸዋል፡፡
መንግሥት ያቀረበው ረቂቅ ከ2017 በጀት አንጻር የ34.4 በመቶ እድገት አለው፡፡
በጀቱ ለዝርዝር እይታ ለፕላን፣ በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ተመርቷል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X