የአፍሪካ የብድር ምዘና ኤጀንሲ በቀጣይ ዓመት ሥራ ሊጀመር ነው
16:11 10.06.2025 (የተሻሻለ: 16:34 10.06.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የአፍሪካ የብድር ምዘና ኤጀንሲ በቀጣይ ዓመት ሥራ ሊጀመር ነው
በግል የተያዘው የደረጃ ምዘና ኤጀንሲ በዓለም አቀፍ ደረጃ አሰጣጦች ላይ ያለውን አድሎአዊነት በመመከት ለአፍሪካ ተስማሚ የሆኑ የብድር ምዘናዎችን ለማቅረብ ያለመ ነው።
ግቦቹ የሚከተሉት ናቸው፦
🟠 የአፍሪካ መንግሥታዊ እና የድርጅት እዳዎችን የአህጉሪቱን መረጃዎች መሠረት በማድረግ በሀገራት ገንዘቦች መመዘን፣
🟠 ገለልተኝነትን ለማረጋገጥ በግል ባለሀብቶች የገንዘብ ድጋፍ መንቀሳቀስ፣
🟠 እ.ኤ.አ 2025 መጨረሻ ወይም በ2026 መጀመሪያ ላይ ሥራ መጀመር።
ኤጀንሲው የሚከተሉትን ለማሳካት አቅዷል፦
🟠 የመረጃ ክፍተቶችን ማጥበብ፣
🟠 ከአህጉሪቱ የልማት ግቦች ጋር የተጣጣሙ የምዘና ዘዴዎችን ማሻሻል፣
🟠 የምዘና አሰጣጥ ወጪዎችን መቀነስ።
ዓለም አቀፍ ኤጀንሲዎችን ከመተካት ይልቅ አፍሪካ በዓለም የካፒታል ገበያዎች ያላትን ደረጃ የሚያጎለብት የበለጠ ሚዛናዊ እና ተዓማኒ አማራጭ ለማቅረብ ያለመ ነው።
በሰው ሰራሽ አስተውሎት የበለፀገ ምሥል
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X