ኢትዮጵያ በቀጣይ የምርት ዘመን 11.6 ሚሊየን ከረጢት ቡና ትሰበስባለች ተባለ
14:31 10.06.2025 (የተሻሻለ: 14:54 10.06.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ኢትዮጵያ በቀጣይ የምርት ዘመን 11.6 ሚሊየን ከረጢት ቡና ትሰበስባለች ተባለ
የአሜሪካ የግብርና ሚኒስቴር ይፋ ያደረገው የፈረንጆቹ 2025/26 የምርት ዘመን ግምት የሀገሪቱ ተስማሚ አየር እንዲሁም መንግሥት በዘርፉ እየተከተላቸው የሚገኙ ፖሊሲዎች በቡና ምርት እና ጥራት ላይ ጉልህ ለውጥ ማምጣቱን አስታውቋል።
የግብርና መሥሪያ ቤቱ የኢትዮጵያን ቡና በተመለከተ ያስቀመጣቸው ግምቶች፦
🟠የምርት ትንበያ፦ በ2025/26 11.6 ሚሊየን ከረጢት ቡና፣
🟠የምርት ሽፋን፦ 790 ሺህ ሄክታር፤ አማካይ ምርት በሄክታር 0.88 ሜትሪክ ቶን
🟠የወጪ ንግድ፦ 7.8 ሚሊየን ከረጢት
🟠የሀገር ውስጥ ፍጆታ፦ 3.7ሚሊየን ከረጢት
ኢትዮጵያ በሁሉን አቀፍ የቡና ልማት ስትራቴጂዋ (2019–2033) በ2033 ከዓለም ሁለተኛዋ ትልቅ የቡና አምራች ለመሆን ወጥናለች። በተጨማሪም ከቡና የወጪ ንግድ በዓመት 4 ቢሊየን ዶላር ገቢ ለማግኘት አስባለች።
በሰው ሰራሽ አስተውሎት የበለፀገ ምሥል
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X