የምስራቅ አፍሪካ ግዙፍ ሳፋሪዎች በዕለታዊ በረራዎች ሊተሳሰሩ መሆኑ ተገለፀ
19:39 09.06.2025 (የተሻሻለ: 19:54 09.06.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የምስራቅ አፍሪካ ግዙፍ ሳፋሪዎች በዕለታዊ በረራዎች ሊተሳሰሩ መሆኑ ተገለፀ
ከሰኔ 8 ጀምሮ የታንዛኒያው ፍላይትሊንክ አየር መንገድ ከታንዛኒያ ቱሪዝም ሚኒስቴር እና ከታንዛኒያ ቱሪስት ቦርድ ጋር በመተባበር በአሩሻ እና በናይሮቢ መካከል ዕለታዊ በረራዎችን ይጀምራል። ይህ በረራ የአፍሪካን ሁለት ታዋቂ የዱር እንስሳ መዳረሻዎች ያለምንም እንከን ያገናኛል።
ሴሬንጌቲ ብሔራዊ ፓርክ፦ ታንዛኒያ
ማሳይ ማራ፦ ኬንያ
⏺ ይህ ዕቅድ የታንዛኒያ ፕሬዝዳንት ሳሚያ ሱሉሁ ሃሰን በክልሉ ቱሪዝምን ለማሳደግ የሚያደርጉትን ጥረት ይደግፋል።
⏺ አሩሻ አውሮፕላን ማረፊያ በተሻሻሉ የጉምሩክ እና የኢሚግሬሽን አገልግሎቶች የክልል ማዕከል ሆኗል። ወደ አካባቢው የሚመጡ ቱሪስቶችን የጉዞ ቅልጥፍና ለማሻሻል የሚያስችሉ የቱርቦፕሮፕ አውሮፕላኖችን ማስተናገድ ይችላል።
⏺ የፍላይትሊንክ ማኔጂንግ ዳይሬክተር ሙናወር ዲራኒ እንደተናገሩት ከታንዛኒያ አየር መንገዶቾ ባለሥልጣን እና ከቱሪስት ቦርድ ጋር የተደረገው የአጋርነት ስምምነት የክልሉን ተፈጥሯዊ እና ባሕላዊ መስህቦች ለማስተዋወቅ የጋራ ቁርጠኝነትን ያሳያል።
በሰው ሰራሽ አስተውሎት የበለፀገ ምሥል
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X