የአፍሪካ የዲጂታል ሉዓላዊነት መንገድ ፣ ሾልከው የሚወጡ መረጃዎችን መቀነስ እና የአካባቢ መሠረተ ልማት ግንባታ

የአፍሪካ የዲጂታል ሉዓላዊነት መንገድ ፣ ሾልከው የሚወጡ መረጃዎችን መቀነስ እና የአካባቢ መሠረተ ልማት ግንባታ
ሰብስክራይብ
የሶቨርኒቲ ሶርስ የዕለቱ ዝግጅት ትኩረቱን በሳይበር ደህነነትን ላይ ሲያደርግ ፣ የአፍሪካ ሀገራት ለዜጎቻቸው የሚሰጧቸዉን ዲጂታል አግልግሎቶችና የተደቀነባቸውን የሳይበር ጥቃቶች በስፋት ይዳስሳል፡፡ ለዚህም ከፍተኛ የሶፍትዌር ኢንጅነር እና የሰዉ ሰራሽ አስተዉሎት አበልፃጊ /ዴቨሎፐር/ አቤል በነበሩን ጋብዘናል፡፡
በአፍሪካ እያደገ የመጣው ዲጂታላይዝ የሆነ አገልግሎት አሰጣጥ ምክንያት በማድረግ የአፍሪካ ሀገራት የሳይበር ደህንነትን በተመለከተ ንቁ የሆነ አካሄድ መከተል ይገባቸዋል፡፡
“ለምሳሌ አሁን ላይ የምንጠቀመው የመረጃ ማዕከል ሊሆን ይችላል፣ ኔትዎርክ ኢንተርኔት ኤክስቼንጅ ፖይንቶቻችንም ሊሆኑ ይችላሉ እንዳሉ ከምዕራባውያን ጋር የተገናኙ ነገሮች ናቸው፡፡ ስለዚህ መጀመሪያ ለእነዚህ ነገሮች መፍትሄ መስጠት፣ ለምሳሌ አፍሪካውያን እንደ አፍሪካ ተቀናጅተው አንድ ኢንተርኔት ኤክስቼንጅ ፖይንት እንዲኖራቸው ሁለተኛ የራሳቸው የመረጃ ማዕከል ቢኖራቸው መረጃ የመውጣቱ ዕድል ይቀንሳል፡፡" ሲል ከፍተኛ የሶፍትዌር ኢንጂነር እና የሰው ሰራሽ አስተውሎት አበልፃጊ ወይም 'ዲቨሎፐር' አቤል በነበሩ ተናግሯል ።
ይህም ከፖርታል ሳይበር ጥቃት ሚስጥራዊ መረጃን ፣ ዲጂታል መሠረተ ልማትን እና አስፈላጊ የህዝብ አገልግሎቶችን መጠበቅ ላይ ሚናው ወሳኝ ነው ፣ ለዚህ ደግሞ ዲጂታል ሉዓላዊነት ሊሰመርበት ይገባል፡፡
‘‘ዲጂታል ሉዓላዊነት - አንድ ሉዓላዊ የሆነ ተቋም የራሱን ፣ ስትራቴጂካዊ መረጃዎችን ወይም ሐብቶችን መጠበቅ እንድትችል ይረዳሃል [....] ይህ ደግሞ የራስን የዲጂታል መሰረተ ልማት መገንባትህ ስለማይቀር ለሀገር ውስጥ ስራ ፈጠራዎችም እድል ይሰጣል’’ ብሏል - ከፍተኛ የሶፍትዌር ኢንጅነር እና የሰዉ ሰራሽ አስተዉሎት አበልፃጊዉ አቤል በነበሩ፡፡
ይህም በመረጃ ሉዓላዊነት ላይ አዎንታዊ ሚናን እንደሚጫወት ባለሙያው ተናግረዋል፡፡
የሳይበር ጥቃት አይነቶች እንዴት ያሉ ናቸዉ ? በታዳጊ ሀገራት ያሉ አገልግሎት ሰጪዎች የሳይበር ጥቃት የሚያጋልጡ ክፍትቶቻቸዉ ምንድን ናቸው ?
ለጥያቄዎቹ መልስ የሚሆኑ እና ሌሎች ሐሳቦችን በሶቨርኒቲ ሶርስስ ላይ ይከታተላሉ።
አዳዲስ ዜናዎች
0