ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ የዲፕሎማሲ አመራር ውስጥ ያላት አበርክቶ እየተለወጠ ለመምጣቱ ብሪክስ ማሳያ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ገለጹ

ሰብስክራይብ

ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ የዲፕሎማሲ አመራር ውስጥ ያላት አበርክቶ እየተለወጠ ለመምጣቱ ብሪክስ ማሳያ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ገለጹ

መሪው ሀገሪቱ ከተለመደው የፖለቲካዊ፣ የሂደት እና የፕሮቶኮል ዲፕሎማሲ ሞዴል እየራቀች መምጣቷን ለኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን በሰጡት ገለጻ ተናግረዋል፡፡

አዲሱ የሀገሪቱ የዲፕሎማሲ ሞዴል በንቁ ተሳትፎ፣ በተለያየ አጋርነት፣ በርዕዮተ ዓለም ነፃነት እና በአጀንዳ መቅረጽ ላይ የተመሠርተ ነው ብለዋል፡፡

ኢትዮጵያ ከፍተኛ የሕዝብ ቁጥር እና ታሪካዊ አሻራ ካላቸው 11 ሀገራት አንዷ በመሆኗ፤ በዓለም መድረክ ላይ ከፍተኛ ሚና መጫወት አለባት ብለዋል።

ሀገሪቱ በብሪክስ ስብስብ ውስጥ የነቃ ተሳትፎ እያደረገች እንደምትገኝም ገልጸዋል፡፡ አክለውም ዲፕሎማሲ በጠንካራ ኢኮኖሚ ሊደገፍ እንደሚገባ አጽንኦት ሰጥተዋል፡፡

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0