ኢትዮጵያ በ2022 የአፍላ ወጣቶችን እርግዝና ለመቀነስ የሚያስችል አዲስ ፍኖተ ካርታ አዘጋጀች
13:24 09.06.2025 (የተሻሻለ: 13:34 09.06.2025)
© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱኢትዮጵያ በ2022 የአፍላ ወጣቶችን እርግዝና ለመቀነስ የሚያስችል አዲስ ፍኖተ ካርታ አዘጋጀች

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ኢትዮጵያ በ2022 የአፍላ ወጣቶችን እርግዝና ለመቀነስ የሚያስችል አዲስ ፍኖተ ካርታ አዘጋጀች
በኢትዮጵያ የስነ-ህዝብ እና ጤና ዳሰሳ ጥናት መሰረት በኢትዮጵያ ከሚገኙ ታዳጊ ልጃገረዶች መካከል 16 በመቶ የሚሆኑት በወጣትነታቸው እንደሚያረግዙ ጥናቶች ይጠቁማሉ። መንግሥት ይህንን ቁጥር እስከ 2022 ዓ.ም ወደ 3 በመቶ ዝቅ የማድረግ ግብ አስቀምጧል።
"የአፍላ ወጣትነት እርግዝና የጤና ጉዳይ ብቻ አይደለም። ከባድ ማሕበራዊና ኢኮኖሚያዊ መዘዞች አሉት" ሲሉ የጤና ሚኒስቴር ደኤታ ደረጀ ዱጉማ መናገራቸውን ጠቅሶ የሀገር ውስጥ ሚዲያ ዘግቧል።
አክለውም ወጣቶችን ታሳቢ ያደረጉ አገልግሎቶችን ማስፋፋት እና በሚገባ የሰለጠኑ የጤና ባለሙያዎችን መመደብ የፍኖተ ካርታው ዋና አካላት መሆናቸውን ጠቁመዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X