የኢትዮጵያ አየር መንገድ የኢትዮ-ሩሲያ ስትራቴጂካዊ አጋርነትን ለማጠናከር ቁልፍ ሚና አለው - የአቪዬሽን ኤክስፐርት

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱየኢትዮጵያ አየር መንገድ የኢትዮ-ሩሲያ ስትራቴጂካዊ አጋርነትን ለማጠናከር ቁልፍ ሚና አለው - የአቪዬሽን ኤክስፐርት
የኢትዮጵያ አየር መንገድ የኢትዮ-ሩሲያ ስትራቴጂካዊ አጋርነትን ለማጠናከር ቁልፍ ሚና አለው - የአቪዬሽን ኤክስፐርት - Sputnik አፍሪካ, 1920, 08.06.2025
ሰብስክራይብ

  የኢትዮጵያ አየር መንገድ የኢትዮ-ሩሲያ ስትራቴጂካዊ አጋርነትን ለማጠናከር ቁልፍ ሚና አለው - የአቪዬሽን ኤክስፐርት

አየር መንገዱ ወደ ሞስኮ የሚያደርገውን በረራ ማስፋቱ የሀገራቱን ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ ግንኙነት ለማጠናከር ዘርፈ ብዙ ፋይዳ አለው ሲሉ የአቪዬሽን ባለሙያው አቶ ዮናታን መንክር ለስፑትኒክ አፍሪካ ገልጸዋል፡፡

"ሞስኮ እና አዲስ አበባ፤ ኢትዮጵያ እና ሩሲያ በጣም ጠንካራ ታሪካዊ ግኑኝነት አላቸው። አሁንም ከሞስኮ ጋር ያለው ትብብር እና አጋርነት እየተጠናከረ በመምጣቱ በጣም ወሳኝ መዳረሻ ሆኖ ቀጥሏል። ስለዚህ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ሞስኮ የሚያደርገውን በረራ መጨመሩ ኢኮኖሚያዊ እና ስትራቴጂካዊ ጠቀሜታ ይኖረዋል።"

ሩሲያ ከአፍሪካ ሀገራት ጋር ያላትን ግንኙነት ለማጠናከር ያላትን ቁርጠኝነት ያደነቁት ኤክስፐርቱ፤ ኢትዮጵያ የብሪክስ አባል ሀገር እንደመሆኗ በግንኙነቱ የሚኖራትን ልዩ ጥቅም ለማስጠበቅ አየር መንገዱ አይነተኛ መሳሪያ መሆኑን አመላክተዋል።

"የኢኮኖሚ እና ንግድ ትብብር ያለ ግኑኝነት አይሠራም። በአዲስ አበባ እና ሞስኮ መካከል ያለው ርቀት ከአየር ትራንስፖርት ውጪ ለየትኛው ዓይነት ጉዞ በጣም እሩቅ ነው። ስለዚህም የአየር ትራንስፖርት ግኑኝነት ላይ መሥራት በጣም ወሳኝ ነው" ብለዋል።

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0