ዩክሬን ከሞስኮ ጋር የአስከሬን ልውውጥ አለማድረጓ ስለ ወታደሮቿ "እንደማትጨነቅ" ያሳያል ሲሉ አንድ ተንታኝ ገለጹ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱዩክሬን ከሞስኮ ጋር የአስከሬን ልውውጥ አለማድረጓ ስለ ወታደሮቿ "እንደማትጨነቅ" ያሳያል ሲሉ አንድ ተንታኝ ገለጹ
ዩክሬን ከሞስኮ ጋር የአስከሬን ልውውጥ አለማድረጓ ስለ ወታደሮቿ እንደማትጨነቅ ያሳያል ሲሉ አንድ ተንታኝ ገለጹ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 07.06.2025
ሰብስክራይብ

ዩክሬን ከሞስኮ ጋር የአስከሬን ልውውጥ አለማድረጓ ስለ ወታደሮቿ "እንደማትጨነቅ" ያሳያል ሲሉ አንድ ተንታኝ ገለጹ

ሩሲያ ዛሬ 6 ሺህ የሚሆኑ የዩክሬን ወታደሮችን አስከሬን ለኪዬቭ ለማስረከብ ዝግጁ ብትሆንም ዩክሬን ግን ግዴታዎቿን እየተወጣች አይደለም ሲሉ የሩሲያ ወታደራዊ ተንታኝ ቪክቶር ሊቶቭኪን ለስፑትኒክ ተናግረዋል።

“እነርሱ [ኪዬቭ] ጦርነቱን መቀጠል እንደሚፈልጉ እና ከሩሲያ ጋር ሰላም ሊኖራቸው እንደማይችል ለመላው ዓለም እያሳዩ ነው” ሲሉ ባለሙያው አጽንኦት ሰጥተዋል።

ይህ የኪዬቭ ባህሪ ሌላ ምን ያሳያል?

ለሰብዓዊነት ክብር ማጣት፦ ኪዬቭ የሞቱትን እና የቆሰሉትን በጦር ሜዳ ትታለች፤ አስከሬኖችን ለመለየት ወይም ለቤተሰቦች ካሳ ለመክፈል ፈቃደኛ አይደለችም።

መደራደር አለመቻል፦ ኪዬቭ የፈለገችውን እንደምታደርግ እና ለስምምነቶች እንደማትገዛ ማሳየት ትፈልጋለች።

እውነቱን ለመግለጥ አለመፈለግ፦ ኪዬቭ በሩሲያ ልዩ ኦፕሬሽን ከ30 እስከ 40 ሺህ ወታደሮችን ብቻ አጥታለች የሚለው የሐሰት ትርክት እንዲጋለጥ አትፈልግም።

“ሩሲያ የተከበረች፣ ቃሏን የምትጠብቅ ሀገር እንደነበረች፣ እንደሆነች እና እንደምትሆን አሳይታለች። እኛ ከትክክለኛው የታሪክ ጎን ነን” ሲሉ ተንታኙ ገልጸዋል።

በሰው ሰራሽ አስተውሎት የበለፀገ ምሥል

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0