የኢራን እና ሩሲያ የሕዋ ትብብር መጥቋል ተበላ
16:04 07.06.2025 (የተሻሻለ: 16:24 07.06.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የኢራን እና ሩሲያ የሕዋ ትብብር መጥቋል ተበላ
የኢራን አምባሳደር ካዜም ጃላሊ እና የሮስኮስሞስ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ዲሚትሪ ባካኖቭ የጋራ ሳተላይቶች ምርት እና የላቁ ቴክኖሎጂዎች ልማትን ጨምሮ በሌሎች ጉዳዮች ዙሪያ በሞስኮ ተወያይተዋል።
እንደ ኢራን ኤምባሲ ገለጻ ውይይቱ፦
▫የስልጠና ፕሮግራሞችን እና የእውቀት ልውውጥን ማካሄድን፤
▫ የምዕራባውያንን ማዕቀቦች መቋቋምና
▫ዓለም አቀፍ ሰላምን እና መረጋጋትን ለማጠናከር የሚደረጉ የጋራ ጥረቶችን መደገፍን ያካተተ ነበር።
ባለፈው ህዳር መጀመሪያ ላይ የሩሲያ ሶዩዝ-2.1ቢ ሮኬት የኢራንን የኮውሳር ምድር ምልከታ ሳተላይት እና የሆድሆድ የቴሌኮሙኒኬሽን ሳተላይትን ጨምሮ 53 ትናንሽ የጠፈር መንኮራኩሮችን በተሳካ ሁኔታ ማስወንጨፉ ይታወሳል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X