ዩክሬን አስከሬን መቀበልንም ሆነ የጦር እስረኞች ልውውጥን ላልተወሰነ ጊዜ ባልተጠበቀ ሁኔታ እንዳራዘመች ሜዲንስኪ ተናገሩ
14:34 07.06.2025 (የተሻሻለ: 14:54 07.06.2025)
© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱዩክሬን አስከሬን መቀበልንም ሆነ የጦር እስረኞች ልውውጥን ላልተወሰነ ጊዜ ባልተጠበቀ ሁኔታ እንዳራዘመች ሜዲንስኪ ተናገሩ

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ዩክሬን አስከሬን መቀበልንም ሆነ የጦር እስረኞች ልውውጥን ላልተወሰነ ጊዜ ባልተጠበቀ ሁኔታ እንዳራዘመች ሜዲንስኪ ተናገሩ
የሩሲያ መከላከያ ሚኒስቴር የግንኙነት ቡድን በዩክሬን ድንበር ቢደርስም የዩክሬን የድርድር ቡድን ወደ ልውውጥ ሥፍራው አልደረሰም።
“ባልታወቀ ምክንያት የድርድር ቡድኑ ወደ ልውውጡ ሥፍራ አልደረሰም። የተለያዩ ምክንያቶች ተጠቅሰዋል፤ ብዙዎቹ በጣም እንግዳ ናቸው” ሲሉ የሩሲያ ባለሥልጣን ተናግረዋል።
የሜዴንስኪ መግለጫ ቁልፍ ነጥቦች፦
▪ሩሲያ ልውውጡን ለመጀመር የመጀመሪያዎቹን 640 የጦር እስረኞች ዝርዝር "ቆሰሉ፣ በጠና የታመሙ እና ወጣቶች" በሚሉ ምድቦች ለዩክሬን አስረክባለች።
▪የመጀመሪያው ዙር 1 ሺህ 212 የዩክሬን ወታደሮች አስከሬን በማቀዝቀዣ መኪናዎች ወደ ልውውጥ አካባቢ ደርሰዋል፤ ቀሪዎቹም በመንገድ ላይ ናቸው።
▪ሩሲያ ኪዬቭ የ6 ሺህ የዩክሬን ወታደሮች እና መኮንኖችን አስከሬን እንድትቀበል ታሳስባለች።
▪ሩሲያ ኪዬቭ በኢስታንቡል የተደረሱትን ስምምነቶች እንድታከብር እና ወዲያውኑ የጦር እስረኞችን ልውውጥ እንድትጀምር ትጠይቃለች።
▪ዓለም አቀፍ የመገናኛ ብዙኃን ከዩክሬን ጋር የጦር እስረኞች ልውውጥ በሚካሄድበት ሥፍራ በመምጣት የሩሲያን ዝግጁነት ማየት ይችላሉ።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X