የአዲስ አበባ የደን ሽፋን 20 በመቶ መድረሱ ተገለፀ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱየአዲስ አበባ የደን ሽፋን 20 በመቶ መድረሱ ተገለፀ
የአዲስ አበባ የደን ሽፋን 20 በመቶ መድረሱ ተገለፀ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 06.06.2025
ሰብስክራይብ

የአዲስ አበባ የደን ሽፋን 20 በመቶ መድረሱ ተገለፀ

ከንቲባ አዳነች አቤቤ "ፅዱ ኢትዮጵያን መፍጠር" በሚል መሪ ቃል የተከበረውን የዓለም የአካባቢ ጥበቃ ቀን አስመልክቶ ባደረጉት ንግግር የከተማው የደን ሽፋን 2 ነጥብ 8 መቶ እንደነበር አስታውሰዋል ሲል የሀገር ውስጥ ሚዲያ ዘግቧል።

አክለውም አስተዳደራቸው በዘላቂ የከተማ ልማት፣ አረንጓዴ ቦታዎችን በማስፋፋት፣ በኮሪደር እና በየወንዝ ዳር ልማት ፕሮጀክቶች መዲናዋን እያስዋበ እንደሚገኝ ተናግረዋል።

የከተማ አስተዳደሩ፦

🟠160 የሕዝብ መናፈሻዎችን፤

🟠 ከ2 ሺህ በላይ የህፃናት መጫወቻ ሥፍራዎችንና

🟠 454 የንፅህና መጠበቂያ በታዎችን በመገንባት በአዲስ አበባ የአረንጓዴ ተነሳሽነቶችን እየተገበረ እንደሚገኝም ገልጸዋል።

ለአካባቢ ተስማሚ የሆኑ ትራንስፖርቶችን በተመለከተ፦

🟠 100 የኤሌክትሪክ አወቶብሶችን፣

🟠 150 አነስተኛ የኤሌክትሪክ አውቶቡሶችን እና

🟠 ለሞተር አልባ እንቅስቃሴ 244 ኪ.ሜ የብስክሌት መንገድ መገንባቱን ተናግረዋል።

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0