የኢትዮጵያ የግብርና ምርቶች የወጪ ንግድ ከ3 ቢሊየን ዶላር ተሻገረ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱየኢትዮጵያ የግብርና ምርቶች የወጪ ንግድ ከ3 ቢሊየን ዶላር ተሻገረ
የኢትዮጵያ የግብርና ምርቶች የወጪ ንግድ ከ3 ቢሊየን ዶላር ተሻገረ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 06.06.2025
ሰብስክራይብ

የኢትዮጵያ የግብርና ምርቶች የወጪ ንግድ ከ3 ቢሊየን ዶላር ተሻገረ

ይህ የተገለፀው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤተ የግብርና ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በግብርና ሚኒስቴርና በተጠሪ ተቋማት የ10 ወራት ዕቅድ አፈጻጸም ላይ ከከፍተኛ አመራሮች ጋር ውይይት ባደረገበት ወቅት ነው።

በግምገማው ወቅት የተነሱ ዋና ዋና ነጥቦች፦

▪ከ400 ሺህ ቶን በላይ ቡና ወደ ውጭ ተልኮ 2 ቢሊየን ዶላር ተገኝቷል።

▪ የአትክልትና ፍራፍሬ ውጤቶች፣ ቅመማ ቅመሞች፣ የቁም እንስሳት እና የእንስሳት ተዋፅኦዎች ገቢ ከተገኘባቸው የግብርና ምርቶች ውስጥ ይካተታሉ።

▪ 31 ሚሊየን ሄክታር በላይ መሬት ለእርሻ ዝግጁ የተደረገ ሲሆን በያዝነው ዓመት 7 ሚሊየን ሄክታር አዲስ የእርሻ መሬት ማካተት ተችሏል።

▪ በአረንጓዴ አሻራ የደን ልማት ከ7 ቢሊየን በላይ ችግኞች የተዘጋጁ ሲሆን 500 ሚሊየን የሚሆኑት ቀድመው ተተክለዋል።

▪ ለመጪው የግብርና ወቅት 24 ሚሊዮን ኩንታል ማዳበሪያ ተገዝቷል፤ ከዚህ ውስጥ 12 ሚሊየን ኩንታል አስቀድሞ ለክልሎች ተሰራጭቷል።

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0