የኢትዮጵያ የግብርና ምርቶች የወጪ ንግድ ከ3 ቢሊየን ዶላር ተሻገረ
16:11 06.06.2025 (የተሻሻለ: 16:34 06.06.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የኢትዮጵያ የግብርና ምርቶች የወጪ ንግድ ከ3 ቢሊየን ዶላር ተሻገረ
ይህ የተገለፀው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤተ የግብርና ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በግብርና ሚኒስቴርና በተጠሪ ተቋማት የ10 ወራት ዕቅድ አፈጻጸም ላይ ከከፍተኛ አመራሮች ጋር ውይይት ባደረገበት ወቅት ነው።
በግምገማው ወቅት የተነሱ ዋና ዋና ነጥቦች፦
▪ከ400 ሺህ ቶን በላይ ቡና ወደ ውጭ ተልኮ 2 ቢሊየን ዶላር ተገኝቷል።
▪ የአትክልትና ፍራፍሬ ውጤቶች፣ ቅመማ ቅመሞች፣ የቁም እንስሳት እና የእንስሳት ተዋፅኦዎች ገቢ ከተገኘባቸው የግብርና ምርቶች ውስጥ ይካተታሉ።
▪ 31 ሚሊየን ሄክታር በላይ መሬት ለእርሻ ዝግጁ የተደረገ ሲሆን በያዝነው ዓመት 7 ሚሊየን ሄክታር አዲስ የእርሻ መሬት ማካተት ተችሏል።
▪ በአረንጓዴ አሻራ የደን ልማት ከ7 ቢሊየን በላይ ችግኞች የተዘጋጁ ሲሆን 500 ሚሊየን የሚሆኑት ቀድመው ተተክለዋል።
▪ ለመጪው የግብርና ወቅት 24 ሚሊዮን ኩንታል ማዳበሪያ ተገዝቷል፤ ከዚህ ውስጥ 12 ሚሊየን ኩንታል አስቀድሞ ለክልሎች ተሰራጭቷል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X