"የሩሲያ ቋንቋ ወደ ኢትዮጵያ የገባው በፍቅር ነው"፦ አያልነህ ሙላቱ
14:14 06.06.2025 (የተሻሻለ: 14:34 06.06.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
"የሩሲያ ቋንቋ ወደ ኢትዮጵያ የገባው በፍቅር ነው"፦ አያልነህ ሙላቱ
በፈረንጆቹ ሰኔ 6 ቀን የሚከበረውን የሩሲያ ቋንቋ ቀን በማስመልከት ከስፑትኒክ አፍሪካ ጋር ቆይታ የነበራቸው ደራሲ እና ሀያሲ አያልነህ ሙላቱ የሩሲያ ቋንቋ ወደ ኢትዮጵያ የገባው በትምህርት ስርዓት ውስጥ እንደ አንድ የውጭ ቋንቋ ስለተዋቀረ ሳይሆን በራሱ ፈቃድ እና ኃይል ነው ብለዋል።
"የሩሲያ ቋንቋ ወደ ኢትዮጵያ ሲገባ ተራማጅ የሆነ አመለካከት ይዞ ነው የገባው፡፡ በሩሲያ ቋንቋ ስትማር የምታገኘው ፑሽኪንን ነው፣ ዶስተዬቭስኪን ነው፣ ቼሃቭን ነው፣ ቶልስቶይን ነው። ይህንን ሥነ-ጽሑፍ በራሱ ቋንቋ ማንበብ ምን ያህል ጠቀሜታ እንዳለው ጉጉት ስለሚያሳድርብህ የአንባብያን ወይም የቋንቋው ተማሪዎች ከእለት ወደለት መጨመሩ አንዱ ይሄ ይመስለኛል" ሲሉ በኢትዮጵያ ስላለው የሩሲያ ቋንቋ ፍላጎት ገልጸዋል።
አክለውም ሩሲያኛን መማር የነጻ ትምህርት እድል ሊያስገኝ መቻሉ አንዱ ትልቁ የስህበት ምክንያት እንደሆነ ተናግረዋል።
"በሶስተኛ ደረጃ ሩሲያ ከኢትዮጵያ ጋር ለረጅም ዘመን ትልቅ የሆነ የወዳጅነት ግንኙነት ያላት፤ በእምነትም በተለያዩ ጉዳዮችም ከኢትዮጵያ ጋርምንም ዓይነት ተቃርኖ የሌላት፤ በታሪክ ሩሲያ የቅኝ ግዛት ስርዓትን ተከትላ መሳሪያዋን ያላነሳች እንዲያውም ቅኝ ገዢዎችን የምትፋለም፣ ለነጻነት የቆመች ሀገር መሆኗን ኢትዮጵያውያን፣ ወጣቱም ያውቃል፡፡ እና ይሄም ራሱ አንድ የሩሲያ ቋንቋን ለማንበብ እና ሩሲያን ለማወቅ የገፋፋ ይመስለኛል፡፡"
በሰው ሰራሽ አስተውሎት የበለፀገ ምሥል
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X